Posts

ቢ ጂ አይ ቢራ ፋብሪካ በ12 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ መሣሪያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

አዋሳ, ህዳር 28 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በሀዋሳ ከተማ የሚገኘው ቢ ጂ አይ ቢራ ፋብሪካ በ12 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ መሣሪያ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታወቀ፡፡ የፋብሪካው ኮርፖሬት ተቆጣጣሪ አቶ በቀለ ሰሙ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ተከላው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው መሣሪያ ፋብሪካው ለቢራ ጠመቃ አገልግሎትና ለጠርሙሰ አጠባ የሚጠቀምበትን ፍሳሽ ከኬሚካል ነጻ በማድረግ በአካባቢ ላይ የሚደርሰውን ብክለት ለመከላከል ያስችላል፡፡ በመሳሪያው አማካይነት ተጣርቶ የሚወጣውን ውሃ በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎች ለመስኖ አገልግሎት መጠቀም እንደሚችሉ ተናግረዋል። ፋብሪካው የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን በመገንባት በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በአንድ ቢሊዮን ብር ካፒታል ተገንብቶ ባለፈው ግንቦት ወር የሙከራ ስራ የጀመረው ቢ ጂ አይ ቢራ ፋብሪካ በአሁኑ ወቅት በቀን 363 ሺህ 600 ጠርሙስ ቢራ በማምረት ላይ የሚገኝ መሆኑን ገልፀው ለ273 ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩንም አስታውቀዋል፡፡ ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምርም የማምረት አቅሙ በእጥፍ እንደሚጨምር አቶ በቀለ ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ክልል ንግድ ኢንደስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሂደት ባለቤት አቶ አበበ ደንጋሞ በበኩላቸው የፍሳሽ ቆሻሻ በአካባቢ ላይ የሚያደርሰውን ብክለት ለመከላከል ፋብሪካው ያከናወነው ተግባር ለሌሎች ፋብሪካዎች አርአያ ሊሆን እንደሚችል አስታውቀዋል፡፡

Kabu Coffee, to Provide Export Standard Ethiopian Coffee

Kabu Coffee has announced plans to market export standard Ethiopian coffee. The company has expanded its investment capital to 10 million birr for this venture. Kabu is marketing high quality roasted coffee to international and domestic customers according to Aman Adinew company advisor. The company aimed to venture out in this direction from the outset he said. Kabu strives to carefully control the quality of its ingredients to ensure the quality service promised by its slogan ‘Coffee Redefined’ said Aman. Adding value to Ethiopia’s number one export, coffee, is sure to make the sector more profitable explains Aman. Ethiopia needs to become competitive in the international roasted coffee market dominated by Europeans he said.  Kabu is partnering with a German firm to introduce roasted and instant coffee into the national market. The company believes that coffee roasted and prepared from Ethiopia and not blended with other types of Coffee will be warmly welcomed on the interna

Debub Global to Enter Ethiopian Banking Sector

Debub Global Bank Share Company is to enter the Ethiopian banking sector in 2012. The Bank has raised 286 million birr in subscribed capital and 150 million in paid up capital through the sale of shares. 5481 shares have been presented to the National Bank pending signature and verification by shareholders according to an official at the Bank. Debub Global Bank expects to concentrate its activities in the South of Ethiopia where there exists untapped potential for investment said the official. The shareholders of the bank understand the potentials in the South and are interested in engaging in investment and trade in the area explained the official. The General Assembly of the bank has presented a list of people who could potentially serve on its board of directors and has waited six months, after meeting all requirements, to begin operations explained the official. The National Bank reviewed the thirty potential nominees to the board of directors according to their credentials

በሲዳማ ዞን ከ113 ሚሊዮን ብር የሚበልጥ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ ተሰጠ

አዋሳ, ህዳር 26 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በሲዳማ ዞን በበጀት አመቱ የመጀመሪያው ሩብ አመት ከ113 ሚሊዮን ብር የሚበልጥ ካፒታል ላስመዘገቡ 25 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የዞኑ ንግድና ኢንደስትሪ መምሪያ ገለጸ። በመምሪያው የኢንቨስትመንት የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ወልደሚካኤል ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ባለሀብቶቹ የሚሰማሩባቸው የስራ መስኮች በግብርና፣ በኢንዱስትሪና ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ለመሰማራት ነው። በሩብ ዓመቱ ፈቃድ የወሰዱት ባለሀብቶች ቁጥር ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት በሁለት ባስመዘገቡት ካፒታል በ30 ሚሊዮን ብር ብልጫ እንደነበረው ገልጸው ባለሀብቶቹ 3 ሺህ ሄክታር መሬት በማግኘታቸው ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ ሲገቡ ከ4 ሺህ 500 ለሚበልጡ ሰዎች የስራ እድል እንደሚፈጥሩ ተናግረዋል። መምሪያው ለባለሀብቶቹ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸው የተሰጣቸው ያላለሙና ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፈው የሰጡ 19 ባለሀብቶች የወሰዱትን ቦታ በመመለስ ፈቃዳችው እንዲሰረዝ ማድረጉን ጠቁመዋል። በዞኑ ወርቅ ታንታለምና የማእድን ውሃና ለተለያየ አገልግሎት የሚውል ሰፊ መሬት እንደሚገኝ ጠቁመው በመስኩ መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች መምሪያው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

በሲዳማ ዞን በወንሾ ወረዳ የተሻሻለ የቡና ዝርያ በመሰራጨት ላይ ነው

አዋሳ, ህዳር 26 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በሲዳማ ዞን በወንሾ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች በሽታና ድርቅን መቋቋም የሚችሉና የተሻለ ምርት የሚሰጡ የቡና ዝርያዎች በመሰራጨት ላይ መሆኑን የወረዳው ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ። የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ በቀለ ሁሞ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በወንዶ ገነት ደን ኮሌጅና በጅማ ግብርና ምርምር ተቋም በአዋዳ ማዕከል በምርምር የተገኙ ከፍተኛ ምርት የሚሰጡና በሽታና ድርቅ መቋቋም የሚችሉ ከግማሽ ሚሊዮን የሚበልጥ ሶስት ዓይነት የሲዳማ ስፔሻሊቲ ቡና ዝርያዎች እየተሰራጩ ነው። በመሰራጨት ላይ የሚገኙት የቡና ዝርያዎች በሁለት አመት ጊዜ ምርት መስጠት የሚችሉና ከነባሩ የቡና ዝርያ ጋር ሲነጻጸር ከ8 እስከ 12 ኩንታል ብልጫ ያለው ምርት በሄክታር መስጨት የሚችል መሆኑን ተናግረዋል። አዲስ በመሰራጨት ላይ የሚገኘው የቡና ዝርያ እስካሁን ከስድስት መቶ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች መሰራጨቱንና በሄክታር ከ20 እስከ 25 ኩንታል ምርት መስጠት እንደቻለ አቶ በቀለ ገልጸዋል። በመጪው ሚያዚያ 2004 ለአርሶ አደሮች የሚሰራጭ ከስድስት መቶ ሺህ በላይ የሲዳማ ስፔሻሊቲ ቡና ችግኝ በመዘጋጀት ላይ መሆኑን ጠቁመው በመንግስት ችግኝ ጣቢያ ብቻ የሚዘጋጀው የቡና ችግኝ በቂ ባለመሆኑ በሞዴል አርሶ አደሮች ማሳ እንዲባዛ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። የቡና ችግኙን በማልማት ላይ ከሚገኙት አርሶ አደሮች መካከል አርሶ አደር አፀደ ጎኔሶ እንደገለጹት በምርምር ከተገኘው የቡና ዝርያ ለሙከራ ወስደው ካለሙት 700 ችግኝ ያገኙት ምርት ከፍተኛ በመሆኑ ችግኙን በብዛት ወስደው ለማልማት ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።

በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አዳማ፤ አዲስ አበባና ሐዋሳ የተሻሉ ተሞክሮዎች ያላቸው ናቸው ተባለ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 21፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አዳማ፤ አዲስ አበባና ሐዋሳ የተሻሉ ተሞክሮዎች ያላቸው ናቸው ተባለ። ሶስተኛው  የከተሞች ቀንን ምክንያት በማድረግ በመቀሌ ከተማ እየተካሄደ ያለው ዝግጅት ዛሬም ቀጥሎ ውሏል። የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን በተመለከተ አየተካሄደ ባለው  የፓናል ወይይት ላይ የኤጀንሲው  ዳይሬክተር አቶ ገብረ መስቀል ጫላ እንደተናገሩት ከተሞች የተሻሉ እንዲሆኑ ያስቻላቸው  የቴክኒክና ትምህርት ሙያና የብድር ተቋማት ጋር በጥምርት በመስራታቸው ነው። ሌሎች የሀገሪቱ ከተሞችም ከእነዚህ በየከተሞቻቸው ከተደራጁት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልምድ  ሊወስዱ ይገባል blewal.

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን የትምህርት ፕሮግራም ከፈተ፤ በአምስት የትምህርት መስኮችም የድህረ ምረቃ ኘሮግራም ሊጀምር ነው

ሃዋሳ, ህዳር 21 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በተያዘው የትምህርት ዘመን የጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን የትምህርት ፕሮግራም በመጀመሪያ ዲግሪ መክፈቱን አስታወቀ፡፡ በአምስት የትምህርት መስኮችም የድህረ ምረቃ ኘሮግራም ሊጀምር ነው፡፡ የዩኒቨርሰቲው የማህበረሰብና ሂዩማኒቲ ኮሌጅ ዲን ዶክተር ንጉሴ መሸሻ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቁት ዩኒቨርስቲው ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን የትምህርት ፕሮግራም ከ30 በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ጀምሯል፡፡ ፕሮግራሙ የተከፈተው ለመማር ማስተማሩ ስራ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች ከተሟሉ በኋላ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በተለይ ተማሪዎች ከንድፈ ሀሳብ ትምህርት በተጨማሪ በተግባር የተደገፈ ልምምድ የሚያደርጉበት በዩኒቨርስቲው የማህበረሰብ ሬዲዮ እንዲሁም ከደቡብ ክልል መንግስት ጋር በመተባበር የክልሉን ኤፍ ኤም ሬዲዮና ቴሌቭዥን ለመጠቀም ምቹ ሁኔታ በመፈጠር ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የፕሮግራሙ መከፈት ብቃት ያለው የመገናኛና የኮሚኒኬሽን ባለሙያ በጥራት በማፍራት ሀገሪቱ ለተያያዘችው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ስኬታማነት አስተዋጾኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡ ከዚህም ሌላ ዩኒቨርስቲው በጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን ፣ እንግሊዘኛን እንደ መነጋገሪያ ቋንቋ ማስተማር ፣ የባህልና ዘርፈ ብዙ የቋንቋዎች ጥናት፣ ሶሻል አንትሮፖሎጂ ፣ ማስታወቂያና ህዝብ ግንኙነት የትምህርት መስኮች የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ለመጀመር ዝግጅት እያደረገ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ ለዚሁ ኘሮግራም የስርዓተ ትምህርት ቀረጻና ግምገማ፣ የመምህራን ምደባና የመሳሰሉ ዝግጅቶች በማካሄድ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ በእያንዳንዱ ፕሮግራምም ከ10 በላይ ተማሪዎችን ተቀብለው እንደሚያሰ

Mugher & Hawassa kick off new EPL season with victories

Image
Mugher Cement FC Addis Ababa, Ethiopia  – Defending champions Ethiopian Coffee were held to a 2-2 draw by the visiting Harar Brewery as the 2011/12 Ethiopia Premier League season kicked off here today. Mugher Cement collected three points with a 2-1 victory in Dire Dawa, while Hawassa City scored narrow win (1-0) at home against the newly promoted Ethiopian Air Force team. The league will continue here tomorrow with two EEPCO vs Sidama Coffee and CBE taking on Adama City. The matches featuring St. George vs Defence Force and Dedebit FC vs Arba Minch City, another newly promoted team, were postponed as they had a number of players selected for the Ethiopian Walia national team, which is currently in Dar es Salaam for the CECAFA Senior Challenge Cup. After one game, Mugher Cement and Hawassa City are in the lead with 3 points and +1 goal. Week 1 Results: Sunday: November 27, 2011 Addis Ababa : Ethiopian Coffee vs Harar Brewery 2-2 Dire Dawa:  Dire Dawa City vs Mug

Ethiopia Premier League: EEPCO 1 Sidama Coffee 0, CBE 1 Adama 1

Image
Published By  Markos Berhanu  On Monday, November 28th 2011. Under  Ethiopian Soccer    Tags:   Addis Ababa , Commercial Bank of Ethiopia ,  EEPCO ,  Ethiopia Premier League    Addis Ababa –  EEPCO kicked off their 2011/12 Ethiopia Premier League season with a 1-0 victory over last year’s Cinderella team, Sidama Coffee. The day’s other double header featuring Commercial Bank of Ethiopia (CBE) and Adama City, ended in a 1-1 draw. The league officially kicked off here yesterday when defending champions Ethiopian Coffee were held to a 2-2 draw by Harar Brewery. The visitors led 1-0 at half-time thanks to a goal by Amha Belete, and it wasn’t until 15 minutes before regulation time that the defending champions equalized through Dawit Estifanos. However, Coffee’s euphoria didn’t last long as Amha Belete hits his second goal two minutes later. The Harari team decided to play a more defensive style to maintain their lead, but Medhane Tadesse scored the equalizer in injury time

የኤርትራን መንግስት አስከፊ ስርዓት ለማስወገድ የሚያስችል አዲስ የስትራቴጂ ትግል የሚቀይስ የኤርትራ ብሄራዊ ጉባዔ ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ውይይት በሐዋሳ ተጀምሯል፡፡

Image
የኤርትራ ኮሚሽን ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ የኤርትራ ተቃዋሚ ኃይሎች ልዩነታቸውን አጥብበው የሀገሪቱን አምባገነን ስርዓት እንዲያስወግዱ ጥሪ አቀረበ ማክስኞ, 22 ህዳር 2011 16:23 የኤርትራ ህዝብ የጭቆና አገዛዝን በመቃወም ለበርካታ ዓመታት የታገለ ቢሆንም ከነጻነትም በኋላ በአምባገነን ስርዓት ለመገዛት ተገዷል፡፡ በውጤቱም የኤርትራ መንግስት በሚከተለው የአፈናና አገዛዝ ሀገሪቱ የሰብአዊ መብት የሚረገጥባትና ዜጎች በአፈና እና በፍርሃት የሚኖሩባት ለመሆን በቅታለች፡፡ በመሆኑም የኤርትራን መንግስት አስከፊ ስርዓት ለማስወገድ የሚያስችል አዲስ የስትራቴጂ ትግል የሚቀይስ የኤርትራ ብሄራዊ ጉባዔ ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ውይይት በሐዋሳ ተጀምሯል፡፡ ጉባዔው ከዚህ በፊት የተቋቋመው የኤርትራ ኮሚሽን ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ባለፉት 16 ወራት የደረሰበትን አፈጻፀም ይገመግማል፡፡ የኤርትራ ኮሚሽን ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ሊቀመንበር አምሃ ዶሞኒካ ፍትህና ዴሞክራሲ የናፈቀውን የኤርትራን ህዝብ ከአምባገነን ስርዓት የማላቀቅ ጊዜው አሁን ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የስርዓቱ በርካታ ተቃዋሚዎች ልዩነታቸውን በማጥበብ የኤርትራን ህዝብ እንዲታደጉት ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስትን አቋም ያቀረቡት የኢህአዴግ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን በኤርትራ ህዝብ ጫንቃ ላይ የተጫነውን አምባገነን አገዛዝ ለማስወገድ የተለያዩ የኤርትራ ተቃዋሚ ኃይሎች አመርቂ ውጤት ማግኘት አልቻሉም፡፡ በመሆኑም የተጀመረው ጉባዔ የነበሩትን ችግሮች በማስወገድ የጋራ ግንዛቤና መግባባት ላይ እንደሚደርስ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል፡፡ በኤርትራ ሰላምና ዴሞክራሲ ለማስፈን ለሚደረገው ትግልም ወንድም የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስትም አስፈላጊው ድጋፍ

Ethiopian Music : Himanot Girma - Lembo

Image
New

Menalush Reta Dayo Bushu Ethiopian Ethiopia Habesha Amharic Music dvd Qu...

Image
New

Ethiopian new 2011 Mulatua Abate, Kai Kai * Sidama s Groove*

Image
New

በደቡብ ክልል መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከሶስት ቢሊዮን በሚበልጥ በጀት የልማት ስራ እያካሄዱ ነው

አዋሳ, ህዳር 5 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በደቡብ ክልል መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በመደቡት ከሶስት ቢሊዮን ብር የሚበልጥ በጀት ህብረተሱቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች በመካሄድ ላይ መሆናቸውን የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ገለጸ፡፡ አብዛኛዎቹ ድርጅቶች የሚንቀሳቀሱት በሀዋሳ ከተማ ፣በሲዳማ ፣ በወላይታ ፣ በጋምጎፋ ፣ በሀዲያና በጉራጌ ዞኖች መሆኑን አስታውቀው የልማት ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ሁሉንም የክልሉ ህዝብ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ታፈሰ ገዳዎ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር እስከ 2015 የሚካሄዱት የልማት ስራዎች 490 ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡ ፕሮጀክቶቹ በ202 መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንደሚካሄዱ አመልክተው የልማት ስራዎቹ የሚያተኩሩት በግብርና ፣በጤና ፣በትምህርት ፣ በመጠጥ ውሃ ፣በመስኖና ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው ዘርፎች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አብዛኛዎቹ ድርጅቶች የሚንቀሳቀሱት በሀዋሳ ከተማ ፣በሲዳማ ፣ በወላይታ ፣ በጋምጎፋ ፣ በሀዲያና በጉራጌ ዞኖች መሆኑን አስታውቀው የልማት ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ሁሉንም የክልሉ ህዝብ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። አፈጻጸማቸውን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ክትትልና ቁጥጥር እንደሚካሄድ ገልጸው መንግስታዊ ያልሆኑት ድርጅቶች ለመንግስት የልማት አጋር በመሆን የአምስት አመቱን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድን ለማሰካት የበኩላቸው አስተዋጾኦ እንዳላቸ ገልጸዋል፡፡

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሰማንያ የሚበልጡ የምርምርና ስርፀት ተግባራትን እያካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ህዳር 2 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሰማንያ የሚበልጡ የምርምርና  ስርፀት ተግባራትን እያካሄደ ነው። ዩኒቨርሲቲው እያካሄዳቸው ያሉ የምርምርና ስርፀት ስራዎች የአካባቢውን ህብረተሰብ  ችግሮች ሊፈቱ የሚችሉ ናቸው። ግብርና፣ ትምህርትና ጤና በምርምርና ስርፀቱ ትኩረት ተሰጥቷቸው  እየተሰሩ ያሉ መሆናቸውን የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ስርፀት ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶክተር ተስፋዬ አበበ ተናግረዋል።

የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ስርጭት ለመጀመር የሚስችል ዝግጅት እያደረገ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28 (ኤፍ ቢ ሲ) የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ስርጭት ለመጀመር የሚስችል ዝግጅት እያደረገ ነው። በሬዲዮ ጣቢያው አስፈላጊነት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ትናንት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የጋራ ውይይት ተካሂዷል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ በዚሁ ወቅት እንዳሉት  የማህበረሰብ ኤፍ ኤም  ሬዲዮ ጣቢያው ስርጭት ዓላማ የተቋሙን የመማር ማስተማር፣ የምርምርና የህብረተሰብ አገልገሎት ለአካባቢው ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ነው፡፡ ጣቢያው ለጊዜው በ50 ኪሎ ሜትር ዙሪያ አገልግሎቱን የሚጀመር ሲሆን ቀስ በቀስም  የስርጭት አድማሱን እንደሚያስፋፋ ጠቁመዋል። 

የሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ግማሽ ቢሊየን ብር በሚሆን ወጭ አዲስ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሊያስገነባ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26 (ኤፍ ቢ ሲ) የሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ግማሽ ቢሊየን ብር በሚሆን ወጭ አዲስ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሊያስገነባ ነው። በአሁኑ ወቅት  የኢንስቲትዩቱን  ግንባታ ለማስጀመር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት የተጠናቀቀ  ሲሆን ስራውም በአንድ  ወር ውስጥ  ይጀመራል  ተብሏል። ግንባታው የተማሪዎች  ማደሪያና የመማሪያ ክፍሎችን  ጨምሮ  ለተለያዩ  አገልግሎቶች የሚውሉ  ህንፃዎችን ያካተተ ነው። በሁለት ዓመት ጊዜ  ውስጥ  የኢንስቲትዩቱ ግንባታ  ሲጠናቀቅ  17 ሺ የነበረውን የዩኒቨርሲቲውን  የተማሪዎች ቅበላ አቅም ወደ 30 ሺ ከፍ እንደሚል በዩንቨርሲቲው የግንባታ ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ደንበሹ ኔኤሬ ለኤፍ ቢ ሲ  ተናግረዋል። እንደ ባልደረባችን ጥላሁን ካሳ ዘገባ የሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ባለፉት 3 አመታት በ480 ሚሊየን ብር ሲያካሂድ የነበረውን የማስፋፊያ ግንባታ ሙሉ በሙሉ አጠናቋል።

South to supply 171,000 tons coffee to central market

South, October 23, 2011 (Hawassa) - Some 171,000 tons coffee will be supplied to the central market from South Ethiopia Peoples' State in the current Ethiopian budget year, the regional marketing and cooperatives bureau said. Speaking at a day long relevant workshop in Hawassa Town of the state on Saturday Deputy bureau head, Abraham Demissie said the amount will exceed by more than double that of same time in the previous budget year. More than 75,440 tons coffee was supplied to market during the last budget year. Abraham said a total of 290,000 tons of coffee is expected to be harvested in the region during the reported period. More than 100 private investors and representatives of associations took part in the workshop

Ethiopia’s Imperfect Growth Miracle

Image
Ethiopia―Africa’s sixth-largest economy and second-most populous nation, home to 90 million people―has recently attracted global attention because of its double-digit economic growth. According to the  Economist , Ethiopia was one of the world’s five fastest-growing economies in 2010. Despite the country’s remarkable growth performance in recent years, however, its record in promoting socio-economic development is mixed. Ethiopia has made significant strides in reducing rural poverty, improving life expectancy, and raising education levels. But these gains have come with rising urban income inequality and surging inflation. It is also not clear whether the services sector, which has accounted for nearly half of GDP growth since 2004, can continue to serve as an economic engine. Impressive Growth Story Since 2004, Ethiopia’s economy has grown by an unprecedented 11 percent on average—up from less than 3 percent annual growth during the previous seven years and much faster than average

Businesses in Hawassa, Ethiopia Begin Using Cash Register Machines

Businesses in Hawassa, capital of the Southern Regional State, started using cash register machines as of last Thursday. VAT registered businesses in the city have transferred from using hand prepared VAT receipts to using the cash registers according to the report. The cash register machines enable VAT registered businesses to abandon the use of VAT receipts except when power outages occur said Seleshi W/Mariam in charge of the tax awareness training process for the regional tax authority. The use of the electronic reporting machines ensures a smooth and speedy relationship between business and the tax authorities he explained. The system also avoids presumptive taxation according to Seleshi. The businesses were offered preparatory training on the use of the machines and the legal and regulatory directives that go with them said Seleshi . The use of the cash register machines in Hawassa is ground breaking for the Southern Regional State said Seleshi. It is expected that the system wi
Image
New

በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር አቶ ማርቆስ ተክሌ አምስት አባላት ያሉት ጃፓን የኢትዮጵያን ቡና እንድትገዛ የሚያግባባ የልዑካን ቡድኑ መርተው ከትናንት በስቲያ ጃፓን ገቡ፡፡

Image
የአሜሪካና የአውሮፓ ኢኮኖሚ ለሁለተኛ ጊዜ አዘቅት ውስጥ እየገባ መሆኑን ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ዋነኛ የውጭ ምንዛሪ ምንጭ የሆነው ቡና ገበያ እንዳያጣ መንግሥትና የቡና ነጋዴዎች አዳዲስ የገበያ መዳረሻዎችን በመፈለግ ሥራ ላይ ተጠምደው ሰንብተዋል፡፡ አዳዲስ የገበያ መዳረሻዎች እንዲሆኑ የተመረጡት ጃፓን፣ ቻይናና ሩሲያ ሲሆኑ፣ ለሥራ ጉዳይ አዲስ አበባ የቆዩት በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር አቶ ማርቆስ ተክሌ፣ አምስት አባላት ያሉት የልዑካን ቡድኑ መርተው ከትናንት በስቲያ ጃፓን ገብተዋል፡፡ የልዑካን ቡድኑ አባላት  በጊዜያዊነት የወጣውን አዲስ ዕቅድ ማለትም የቡና ነጋዴዎች ከገበሬዎች ሰብስበው በምርት ገበያ በኩል ከሚቀርበው ቡና በተለየ ሁኔታ፣  በዩኒየኖችና  በኢንቨስተሮች የሚቀርበውን ቡና ጃፓን እንድትገዛ ለማግባባት ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልከው የቡና መጠን ውስጥ 20 በመቶ የሚሆነውን ትገዛ የነበረችው ጃፓን፣ በቡና ውስጥ ለጤና ጠንቅ የሆኑ ኬሚካሎችን አግኝቻለሁ በሚል ቡና ከኢትዮጵያ መግዛቷን በማቋረጧ ነው፡፡ የተቋረጠውን ግብይት ለማስጀመር ኢትዮጵያና ጃፓን ባለፉት ጊዜያት በጉዳዩ ላይ ሲወያዩ ቆይተዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት ኢትዮጵያ በያዘችው አቋም ጃፓን ኬሚካሉን ያገኘችው ከኢትዮጵያ ወደ አውሮፓ ከተላከ ቡና እንጂ፣ በቀጥታ ከኢትዮጵያ ወደ ጃፓን ከተላከ ቡና ውስጥ አይደለም፡፡ ኬሚካል ተገኘበት የተባለው ቡና ደግሞ በጉዞና በተለያዩ ምክንያቶች ጃፓን እስኪደርስ ድረስ ስምንት ወራት የቆየ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያ ልትጠየቅ አይገባም የሚል መከራከርያ ቀርቧል፡፡ ይሁንና ጃፓን የኢትዮጵያን ቡና መግዛት በማቋረጥ ከቡና ውስጥ አራት ዓይነት የኬሚካል ይዘቶችን ስትመረምር ቆይታለች፡፡ በአሁኑ ወቅት ሦስት ኬሚካሎችን በቡናው ውስጥ ባለማግ

ጃፓን ለሲዳማ ዞን የገንዘብ ድጋፍ ሰጠች

አዲስ አበባ, መስከረም 18 ቀን 2004 (አዲስ አበባ) - ጃፓን በኢትዮጵያ በሰብአዊ ደሕንነት ላይ ለሚካሔዱ ሁለት ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ የሚውል የ225 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ሰጠች፡፡ የገንዘብ ድጋፉን ለመስጠት ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ የጃፓን ኤምባሲ ከሲዳማ ዞን እና ሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎፕመንት ከተሰኝ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር ተፈራርሟል፡፡ ስምምነቱን በጃፓን በኩል የፈረሙት በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሒሮዩኪ ኪሽኖ፣ የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪው አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ እንዲሁ የሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎመንት ዳይሬክተር አቶ በላቸው ለማ ናቸው፡፡ የጃፓን መንግስት ለሰብአዊ ድህነነት ስራዎች ትኩረት የሚሰጥ ሲሆን ድጋፉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች እንደሚው አምባሳደሩ ጠቁመዋል ጃፓን ከ1997 ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ በትምህርት፣ በመጠጥ ውሃና በሌሎችም መሰረታዊ የሰው ልጅ ፍላጎትን በሚያሟሉ ዘርፎች ከ300 በላይ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጓን አብራርተዋል፡፡ የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ እና የሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎመንት ዳይሬክተር አቶ በላቸው ለማ በዚሁ ወቅት የገንዘብ ድጋፉን በአግባቡ ለተፈቀደለት ስራ በማዋል ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡

በብሔራዊ ባንክ ብቻ ይሰጥ የነበረው የወርቅ ግዥ ሥርዓት በሐዋሳ መስጠት ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ, መስከረም 18 ቀን 2004 (አዲስ አበባ) - በብሔራዊ ባንክ ብቻ ይሰጥ የነበረው የወርቅ ግዥ ሥርዓት ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በክልል አራት ከተሞች አገልግሎት መሰጠት እንደሚጀመር የማዕድን ሚኒስትሯ አስታወቁ፡፡ የማዕድን ሚኒስትር ወይዘሮ ስንቅነሽ እጅጉ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በአገር አቀፍ ደረጃ የወርቅ አቅርቦት መጠን እየጨመረ በመመጣቱ በብሔራዊ ባንክ ብቻ ይሰጠው የነበረውን ግዥ ወደ ምርት አካባቢዎች ማስፋት አስፈላጊ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በመሆኑም ሚኒስቴሩ ወርቅ ከሚመረትባቸው ክልሎች መካከል በሐዋሳ፣ በጅማ፣ በመቀሌና በአሶሳ በሚገኙ የኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች ግዥውን ሥርዓቱ ከሚቀጥለው ሳምንት በይፋ እንደሚጀመር ገልጸዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለብሔራዊ ባንክ የቀረበው የወርቅ መጠን ሰባት ቶን የነበረ ሲሆን፣ በያዝነው ዓመት ግን ምርትና አቅርቦቱ ከ13 ቶን በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል፡፡ በክልሎች የወርቅ ግዥ ጣቢዎች መክፈት ወርቅ አቅራቢዎች ወደ አዲስ አበባ ያደርጉት የነበረውን ረጅም ጉዞ ከማስቀረቱ ባሻገር፤ ፈጣንና ቀልጣፋ የግዥ ሂደት ለመፍጠር እንደሚያስችል ሚኒስትሯ አስረድተዋል፡፡ በተለይ ወርቅ አምራች የኅብረት ሥራ ማህበራት በአቅራቢያቸው ወርቅ የሚሸጡባቸው የግዥ ማዕከላት ባለመኖራቸው ለሌላ ገዢ በመሸጥ ማግኘት የሚገባቸውን ጥቅም ሳያገኙ መቆየታቸን ወይዘሮ ስንቅነሽ ገልጸዋል፡፡ በአራቱ ከተሞች የግዥ አገልግሎቱ ሲጀመር ግን የወርቅ አቅራቢዎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ይሆናል ብለዋል፡፡ በክልል ከተሞች በሚካሄደው የወርቅ ግዥ ሥርዓት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ በአዲስ አበባ ማዕከል የሚሰጡትን ዓይነት አገልግሎት እንደሚሰጡም ሚኒስትሯ አመልክተዋል፡፡ በነዚህ የግዥ ጣቢያዎች

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የሚመጡ ተማሪዎችን በሁለተኛ ዲግሪ እንዲያሰለጥን ተመረጠ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10 2004 (ኤፍ ቢ ሲ)የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት  የሚመጡ ተማሪዎችን በሁለተኛ ዲግሪ ተቀብሎ እንዲያሰለጥን ተመረጠ።         ዩኒቨርሲቲው በሁለተኛ ዲግሪ ስልጠና ለመስጠት የተመረጠው ከዘጠኝ የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ተወዳድሮ ብቁ ሆኖ በመገኘቱ ነው። የዩኒቨርሲቲው ማርኬቲንግና ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ መልሰው ደጀኔ ለኢ ዜ አ እንዳሉት ስልጠናው የሚሰጠው በ11 የተለያዩ ፕሮግራሞች ነው። ዩኒቨርሲቲው ስልጠናውን የሚሰጠው  በአውሮፓ ታዋቂ ከሆነው ኢራስመስ ከተባለው ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ፣ የካሪቢያንና የፓስፊክ ፕሮግራም ማዕቀፍ ጋር በመተባበር ነው።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ለከተማው አዲስ ከንቲባ ሾመ

  አዋሳ, ነሐሴ 30 ቀን 2003 (ሃዋሳ) - በደቡብ ሕዝቦች ክልል የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ሶስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባዔ ዛሬ ተጀመረ፡፡ ምክር ቤቱ ጉባኤውን ሲጀምር ለሀዋሳ ከተማ ከንቲባነት በሙሉ ድምጽ የሾማቸው አቶ ዮናስ ዮሴፍ ቀደም ሲል የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ የነበሩ ናቸው። አዲሱ ከንቲባ ቀደም ሲልም በሲዳማ ዞን የዳሌ ወረዳ አስተዳዳሪ ፣የሲዳማ ዞን ትምህርት መምሪያ ሃላፊ በመሆን ያገለገሉ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ ምክር ቤቱ ሾመቱን የሰጠው ቀደም ሲል የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በነበሩት በአቶ ሽብቁ ማጋኔ ምትክ መሆኑም ተገልጿል፡፡ የከተማው ምክር ቤት ጉባኤ የ6ኛ መደበኛ ጉባኤውን ቃለ ጉባኤ መርምሮ በማጽደቅ በሶስት ቀናት ቆይታው በ2003 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ፣በ2004 በጀት ዓመት ዕቅድና በጀት ላይ ተወያይቶ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡

በሀዋሳ ከተማ ወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልገሎት ስራ አከናወኑ

አዋሳ, ነሐሴ 30 ቀን 2003 (ሃዋሳ) - በሀዋሳ ከተማ ለሁለት ወራት በተካሄደ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልገሎት ከሁለት ሚልዮን ብር የሚበልጥ ግምት ያለው ስራ መሰራቱን የከተማው ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ ገለጸ፡፡ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ ትናንት በሀዋሳ ከተማ ሲካሄድ ምክትል መምሪያ ሃላፊው አቶ በላይ ዲካ እንደገለጹት በከተማው ስምንት ክፍለ ከተሞች 36 ሺህ 155 ወጣቶች ነፃ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ከተሳተፉት ወጣቶች መካከል ስምንት ሺህ 903 ሴቶች መሆናቸውን ገልጸው ወጣቶቹ በማጠናከሪያ ትምህርት፣ በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ችግኝ ተከላ፣ በጤና፣ በአረጋውያንና ወላጅ አልባ ህፃናት ድጋፍ ላይ ያበረከቱት አስተዋፅኦ 2 ሚልዮን 57 ሺህ 150 ብር መገመቱን አስታውቀዋል፡፡ ወጣቶቹ ከራሳቸውና ሌሎች ወገኖች አልባሳትና የፅህፈት መሳሪያ በማሰባሰብ ለ3 ሺህ 160 አረጋውያንና ወላጅ አልባ ህፃናት ከማከፋፈላቸው በተጨማሪ የስምንት አረጋውያንን መኖሪያ ቤት መጠገናቸውን ገልጸዋል፡፡ የደቡብ ክልል ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ቢሮ ምክትል ሃላፊና የሴቶችና ህፃናት ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ህይወት ሃይሉ እንዳሉት ወጣቶቹ በእረፍት ጊዜያቸው ያበረከቱት አገልግሎት ለማህበረሰቡ ካስገኙት ጠቀሜታ በተጨማሪ የህይወት ክህሎት ትምህርት የቀሰሙበት ነበር፡፡ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ተወካይ አቶ ታዬ ቢሊሶ በከተማው እየተከናወነ ያለው የልማት ስራ ቀጣይ እንዲሆን ወጣቱ በበጎ ፈቃድ አገልገሎት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበው የከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልገሎት ተሳታፊ ለሆኑ ወጣቶችና ድጋፍ ላደረጉ መንግስታዊና መንግስ

Ethiopian diaspora in US to build trade center worth 127m Birr in Hawasa.

South Ethiopia Community members living in United States (US) are to build a trade center worth 127 million Birr in Hawasa town. Representatives of the Community members and government officials on Thursday held a panel discussion in ERTA studio on ways of advancing development participation for Ethiopian diaspora. On the discussions, South Ethiopia Community President in US, Abbas Hussien said members of the Community have finalized preparations to build the trade center in Hawasa town. He said the Community is receiving the necessary support from the government, in an organized activity about 200 members are undertaking to be part of the ongoing development endeavors at home. Government officials participated in the discussions stated efforts made by the government to boost development participation of Ethiopian diaspora.

How Hawassa is changing

New

በደቡብ ክልል በተጠናቀቀው የትምህርት ዘመን በትምህርት ልማት ዘርፍ የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ የትምህርት ልማት ሰራዊቶች ተሸለሙ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 7 2004 (ኤፍ ቢ ሲ)በደቡብ ክልል በተጠናቀቀው የትምህርት ዘመን በትምህርት ልማት ዘርፍ  የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ከ100 በላይ የትምህርት ልማት ሰራዊቶች ተሸለሙ። በሃዋሳ ከተማ ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው 17ኛው አጠቃላይ የትምህርት ጉባኤ የላቀ ውጤት  ላስመዘገቡ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ትምህርት ቤቶችና የትምህርት ጽህፈት ቤቶች የማበረታቻ ሽልማት  በመስጠት ዛሬ ማምሻውን ተጠናቋል። ለተሸላሚዎቹም የዋንጫ፣ የሜዳሊያ የቦንድና የተለያዩ ቁሳቁሶችን በሽልማት ተሰጥቷል። የጉባኤው ተሳታፊዎች ባወጡት የአቋም መግለጫ መላውን ህብረተሰብ በላቀ ሁኔታ በማነቃቃት  የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናትን በሙሉ ወደ ትምሀርት  ቤት ለማምጣት በግንባር ቀደምትነት ለመንቀሳቃስ ቃል መግባታቸውን ባልደረባችን ሰለሞን ገመዳ ከሃዋሳ ዘግቧል። 

የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ለ 5 ሺ 671 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

አዲስ አበባ፣ጳጉሜን 5 ፣ 2003 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት አዲሱን  ዓመት ምክንያት በማድረግ ለ 5 ሺ 671 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በተለያየ የወንጀል ድርጊት  ተከሰው በፍርድ ማረሚያ ቤት ከቆዩ የህግ ታራሚዎች መካከል ይቅርታ የተደረገላቸው የባህሪ ለውጥ  ያመጡና የእስራት ጊዜያቸውን ያገባደዱ ናቸው ። የተደረገው ይቅርታ በሙስና ፣በአስገድዶ መድፈር፣ በዘር ማጥፋትና በግፍ በሰው ህይወት ማጥፋት ክስ  ተመስርቶባቸው የተፈረደባቸውን እንደማይመለክትም አስታውቀዋል። ይቅርታ የሚደረግላቸው ታራሚዎች ወደ ህብረተሰቡ ሲቀለቀሉ ዳግመኛ በወንጀል ድርጊት ባለመሳተፍ  የበደሉትን ህዝብና መንግሰት መካስ እንዳለባቸው ነው የሳሰቡት። ህብረተሰቡም ይቅርታ ለተደረገላቸው ታራሚዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።

በደቡብ ክልል የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ ሊሰጠን ይገባ የነበረውን የስራ ደረጃ ዕድገት አላገኘንም አሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ)  በደቡብ ክልል የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች  አምና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከተደረገው የደመወዝ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ ሊሰጠን ይገባ የነበረውን  የስራ ደረጃ ዕድገት አላገኘንም አሉ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ  ቢሮ ሀላፊ አቶ አቶ ደበበ አበራ በበኩላቸው ችግሩ መሰረታዊ የአሰራር ሂደት ተግባራዊ ሲደረግ የተከሰተ እንደሆነ ተናግረዋል። ሰራተኞቹ ለኤፍ ቢ ሲ ሪፖርተር እንደነገሩት ከደመወዝ ጭማሪው ጋር ተያይዞ በክልሉ የመሰረታዊ  የአሰራር ሂደት ለውጥ ተግባራዊ ቢደረግም ምደባው ችግር አለበት  ነው የሚሉት። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ሀላፊ አቶ አቶ ደበበ አበራ በበኩላቸው  ችግሩ መሰረታዊ የአሰራር ሂደት ተግባራዊ ሲደረግ የተከሰተ እንደሆነ ተናግረዋል። በ15 ቀናት ውስጥ ቅሬታዎቹ ምላሽ እንደሚያገኙም ነው ያስታወቁት። በመላው ሀገራችን የሰራተኛውን ገቢና የኑሮ ውድነት ታሳቢ በማድረግ መንግስት  በ2003 አጋማሽ ላይ ለሁሉም የመንግስት ሰራተኛ የደመወዝ ጭማሪ አድርጓል። ይህም በሁሉም የመንግስት ሴክተር መሰሪያ ቤቶች ነው ተግባራዊ የተደረገው። ከዚህው ጋር በታያያዘም የሰራተኛው የደረጃ እድገት በአብዛኞቹ ክልሎች ተግባራዊ ተደርጓል። የደቡብ ክልል የመንግስት ሰራተኞች ቅሬታ አምና ተግባራዊ ከተደረገው የደመዎዝ ጭማሪ  ጋር በተያያዘ የስራ ደረጃ አመዳደብ ጋር ይያያዛል። ሰራተኞቹ የሚያነሷቸው ቅሬታም የስራ ደረጃ ዕድገቱ ፍትሃዊ አይደለም የሚል ነው።  ሰራተኞቹ አሉ የሚሏቸውን ችግሮች ያነሳሉ። በሌሎች ክልሎች ተግባራዊ መደረጉንም ያነሳሉ። ክልሉ አስቸኳይ መፍትሄ ይፈልግልን ነው የሚሉት። አቶ ደበበ አበራ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳርና የቢሮው ሀላፊ ናቸው። በሀገር

ከቻይና የመጣ የልኡካን ቡድን በሀዋሳ ከተማ የተቋቋመውን የኢንዱሰትሪ መንደር ጎበኘ፡፡

ከቻይና የመጣ የልኡካን ቡድን በሀዋሳ ከተማ የተቋቋመውን የኢንዱሰትሪ መንደር ጎበኘ፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ከቻይና ቾንቺን ግዛት ለመጣው የልኡካን ቡድን እንደገለጹት  የበርካታ ብሄር ብሄረሰቦቸና ህዝቦች መኖሪያ የሆነው የደቡብ ክልል በኢንዱሰትሪ፣ ግብርናና አገልግሎት ተቋማት  መሳተፍ ለሚፈልጉ ባለሃብቶች ዕምቅ ሃብት ይገኝበታል፡፡ በክልሉ 22 የሪፎረም ከተሞች የመሰረተ ልማት አገልገሎት የተሟላላቸው የኢንዱሰትሪ መንደሮች መዘጋጀታቸውን ገልጸው በኢንዱስትሪ ዘርፍ መስራት ለሚፈልጉ ባለሃብቶች የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል፡፡ በክልሉ ካለው ምቹ ሁኔታ በመታገዝ ብዛት ያላቸው ባለሃብቶች መዋዕለ ንዋያቸውን አፍስሰው እየሰሩ መሆኑን ገልጸው  በክልሉ በማንኛውም መሰክ መሰማራት ለሚፈልጉ የቻይና ባለሃብቶችን ለመቀበል የክልሉ መንግስት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከቻይና የቾንቺን ግዛት የመጡት የልዑካን ቡድን ተወካይ የክልሉ መንግስት ላደረገላቸው አቀባበል አመስግነው የቻይናው ሊፋን ኢንዱስትሪ ፓርክ በሀዋሳ የመኪና አካላት ማምረቻና መገጣጠሚያ መንደር ለማቋቋም የተለያየ  ስራ እየተካሄደ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የቾንቺን ግዛት በርካታ ኢንዱስትሪ የሚገኙበት መሆኑ

Hawassa University to enroll 5000 new students

Hawassa, July 23, 2011 (Hawassa) - Hawassa University in South Ethiopia Peoples' State expressed readiness to enroll more than 5000 new students in the coming academic year. University's Planning and Program Department Head, Dr. Tsegaye Bekele told ENA on Friday that most of the construction of expansion projects launched for the university has been completed. Dr. Tsegaye said the government allocated 540 million Birr budget for construction of the projects. The projects include, among others, construction of classrooms, dormitories, library, laboratory and offices. Preparations necessary for the learning-teaching process have been finalized, he said, adding, special attention has been given to provide support to girl students. The university is undertaking preparation to launch new programs including in journalism field of study. Over 470 million Birr is allocated to carry out additional expansion projects. The expansion project will help the university to increas

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በመጪው የትምህርት ዘመን ከአምስት ሺ በላይ አዲስ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሀምሌ 16 2003 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በመጪው የትምህርት ዘመን ከአምስት ሺ በላይ አዲስ ተማሪዎችን ለመቀበል  ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ። ዩኒቨርሲቲው በትምህርት ዘመኑ ከሚቀበላቸው ተማሪዎች 70 በመቶዎቹን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ቀሪዎቹ ደግሞ  በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፎች ለማሰልጠን ነው የተዘጋጀው።  አዲስ ለሚቀበላቸው ተማሪዎች በ540 ሚሊዮን ብር ከተጀመሩት 33 ነባር  የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች አብዛኛዎቹ ተጠናቀው ለአገልግሎት መዘጋጀታቸውንም ገልጿል። በየትምህርት ዘርፉ የሚያስተምሩ መምህራንና መጻህፍት ማሟላትን ጨምሮ ሌሎችም ለመማር ማስተማሩ ስራ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል። ዩኒቨርሲቲው ለተጨማሪ የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ግንባታ ማስፈጸሚያም ከ470 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡንም አስታውቋል።  ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በመደበኛና በተከታታይ የትምህርት ፕሮግራሞች 23 ሺ የሚጠጉ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ እንደሚገኝ የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።