የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ስርጭት ለመጀመር የሚስችል ዝግጅት እያደረገ ነው


አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28 (ኤፍ ቢ ሲ) የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ስርጭት
ለመጀመር የሚስችል ዝግጅት እያደረገ ነው።
በሬዲዮ ጣቢያው አስፈላጊነት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ትናንት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የጋራ
ውይይት ተካሂዷል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ በዚሁ ወቅት እንዳሉት  የማህበረሰብ ኤፍ ኤም 
ሬዲዮ ጣቢያው ስርጭት ዓላማ የተቋሙን የመማር ማስተማር፣ የምርምርና
የህብረተሰብ አገልገሎት ለአካባቢው ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ነው፡፡
ጣቢያው ለጊዜው በ50 ኪሎ ሜትር ዙሪያ አገልግሎቱን የሚጀመር ሲሆን ቀስ በቀስም 
የስርጭት አድማሱን እንደሚያስፋፋ ጠቁመዋል። 

Comments

Popular posts from this blog

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ