Posts

ስጋት ያጠላበት የሃዋሳ ሃይቅ

Image
ከአለት ጋር እየተጋጨ የሚመለሰው ውሃና ቁር ቁር የሚለው የእንቁራሪቶች ድምፅ  ሀይቁን አጅበውታል፡፡ ወጀብም አልነበረውም፡፡ አልፎ አልፎ በውስጡ የበቀሉ ይታያሉ፡፡ ሀይቁ ዳርና ዳር የሰፈሩት ሌዊና ሀይሌ ሪዞርት ለሃዋሳ ሀይቅ ልዩ ድባብ ሆነውታል፡፡ በመብራትና በተለያዩ እፅዋት የደመቀውን የሪዞርቶቹን ድባብ ሀይቁም ተጋርቷቸዋል፡፡  ሀይቁም ለሪዞርቶቹ ልዩ ግርማ ሞገስ ሆኗቸዋል፡፡ ጀምበር መጥለቅ ስትጀምር በሀይቁ ላይ የሚኖረው እንቅስቃሴ አብሮ ይቀዘቅዛል፡፡ ጥንድ ጥንድ ሆነው የሚዝናኑ ፍቀረኛሞችንና ጎብኚዎችን ይዘው ቀኑን ሙሉ ሀይቁን ሲቀዝፉ የሚውሉ ጀልባዎችም ጥግጥጉን ይይዛሉ፡፡ በውሃ ግፊት ቦታቸውን እንዳይለቁም ከቃጫ በተሰራ ገመድ ከአለቶችና ከዛሆች ጋር ታስረዋል፡፡ ፍፁም ሰላም የሰፈነበትን ሃይቁን በተመስጦ የሚያዩና በዙሪያው የሚዝናኑ እዚህም እዚያም ይታያሉ፡፡ በስልካቸው ፎቶ የሚነሱም ብዙ ናቸው፡፡ ለአይን ያዝ ሲያደርግ ብዙ ደንበኞች አይገኙምና አልፎ አልፎ ብቅ የሚሉ ደንበኞችን ቀድሞ ለመውሰድ የሚደረገው ሽሚያ ቀልብ ይስባል፡፡ በአዋሳ ፍቅር ሀይቅ ዙሪያ ያሉትን መዝናኛና ምግብ ቤቶች አልፈው ወደ ሀይቁ ከመጠጋትዎ ደንበኛ በሚሻሙ የጀልባ ካፒቴኖች ይከበባሉ፡፡ በየርቀቱ የሚያስከፍሉት ዋጋ ተመሳሳይ ቢሆንም፣ ደንበኛው አንዱን እስኪመርጥ ዋጋቸውን ደጋግመው ይነግሩዎታል፡፡ የት መሄድ እንደሚፈልጉም በጥያቄ ያዋክቡዎታል፡፡ አንዱን እንደመረጡ ትተዎት ይበታተናሉ፡፡ ሌላ ደንበኛ መጠባበቅም ይጀምራሉ፡፡ ዋና ለማይችሉ ሰዎች በጀልባ መጓዝ የሚያስጨንቅ ስሜት ይፈጥራል፡፡ በተለይም በተፈጥሯቸው ውሀ ለሚፈሩ ሰዎች ጭንቀቱ ከባድ ነው፡፡ ሀዋሳ ደርሶ ሀይቁን በጀልባ ሳያቋርጡ መመለሱ ያስቆጫልና ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን ለመቀነስ ጀልባው ውሀ ያስገባል?

ወደ ውጪ ከሚላከው ቡና ገሚሱን ቆልቶ በመላክ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ እየተሰራ ነው

Image
(ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ዓመታት ወደ ውጪ ከምትልከው ቡና ግማሽ ያህሉን ሀገር ውስጥ ቆልታ በመላክ ከዘርፉ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ እየሰራች መሆኑን ተገለፀ። የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ልማት ግብይት ባለ ስልጣን በቡና ላይ እሴት ጨምሮ መላክ የተጀመረ ቢሆንም፥ በቀጣይ ከሚመረተው ቡና 50 በመቶ ያህሉን እሴት ጨምሮ ለመላክ የሚያስችሉ ስራዎች ከወዲሁ እየተሰሩ ነው ብላዋል። የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሻፊ ኡመር የቡና ምርትን ለማሳደግ የሚያስችሉ አዳዲስ የቡና አብቃይ አካባቢዎች እየተለዩ እንዳሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ 25 በመቶ የወጪ ንግዷ በቡና የሚሸፈን ሲሆን 708 ሺህ ሄክታር መሬት በቡና እየለማ ነው።  በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት 270 ሺህ ቶን ቡና ለዓለም አቀፉ ገቢያ በማቅረብ 1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዷል። ባለስልጣኑ የዘንድሮ እቅዱን ለማሳካት ዓለም አቀፍ የቡና አውደ ርእዮች ላይ በመሳተፍ የኢትዮጵያ ቡና ፈላጊ ሀገራት ቁጥርን ለማሳደግ እንደሚሰራ ማስታወቁን ይታወሳል።   ባለፈው ዓመትም 225 ሺህ ቶን ቡና ለውጭ ገበያ ቀርቦ 882 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ መገኘቱ ይታወቃል።

በኦሮሚያ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ 30 ሰዎች ሞተዋል

Image
240 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል በኦሮሚያ ክልል በቡኖ በደሌ ዞንና በአምቦ ከተማ በአንድ ሳምንት ውስጥ 30 ሰዎች ሲሞቱ፣ 37 ያህል ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ በቡኖ በደሌ ዞን በገቺ፣ በደሌ፣ ጮራና ዴጋ ወረዳዎች ጥቅምት 12 ቀን 2010 ዓ.ም. ግጭት መቀስቀሱ የሚታወስ ሲሆን፣ በዚህ ግጭት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 20 መድረሱ ተገልጿል፡፡ በግጭቱ ምክንያት ወደ ሥፍራው አቅንተው የነበሩት የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሡ ጥላሁን ጥቅምት 17 ቀን 2010 ዓ.ም. ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ግጭቱ በተቀሰቀሰበት ወቅት የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ስለነበሩ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ሊጨምር ችሏል፡፡ በወቅቱ 14 ሰዎች መሞታቸውን፣ ከሃምሳ በላይ ቤቶች መቃጠላቸውን፣ በ14 ሰዎች ላይ ከፍተኛ የአካል ጉዳት መድረሱን፣ 1,500 መፈናቀላቸው መዘገቡ ይታወሳል፡፡ አሁን በደረሰው መረጃ መሠረት 20 ሰዎች ሲሞቱ፣ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 14 ቢሆኑም፣ የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ግን ከሦስት ሺሕ በላይ እንደሆነ አቶ ንጉሡ ገልጸዋል፡፡ አቶ ንጉሡ እንዳሉት ግጭቱ በተከሰተበት ዞን በአብዛኛው ሕይወታቸውን ያጡት የኦሮሚያ ክልል ተወላጆች ናቸው፡፡ የአማራ፣ የትግራይና የደቡብ ክልሎች ተወላጆችም ሕይወታቸውን እንዳጡ አክለዋል፡፡ የዚህ ግጭት ዋነኛ ምክንያት ምንድነው ተብሎ ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ንጉሡ፣ ‹‹በኦሮሚያ ክልል ኅብረተሰቡ ቅሬታውን በሠልፍ እንደሚገልጽ እያስተዋልን ነው፡፡ ይህም አካባቢ ሠልፍ ከሚካሄድባቸው መካከል አንዱ እንደሆነ አይተናል፡፡ ሠልፉም በሰላማዊ ሁኔታ እንደተጠናቀቀ ሰምተናል፡፡ ነገር ግን ሠልፉ ከተካሄደ በኋላ ወደ ዘረፋና ብጥብጥ ነው ያመራው፡፡ ሕዝቡ ሠልፉን በሰላም

“ቅድሚያ ለስፖርታዊ ጨዋነት” የግንዛቤ ማስጨበጫ እና ውይይት መድረክ በሀዋሳ ተካሄደ

Image
“ቅድሚያ ለስፖርታዊ ጨዋነት” በሚል መርህ በሀዋሳ የስፖርታዊ ጨዋነት ግንዛቤ ማስጨበጫ እና ውይይት መድረክ በደቡብ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ እና በክልሉ እግርኳስ ፌድሬሽን ትብብር አርብ በኃይሌ ሪዞርት ተካሂዷል፡፡ መድረኩን ለማዘጋጀት የታሰበው ጥቅምት 17 እና 18 ቢሆንም አርብ ከጠዋት ጀምሮ እስከ ምሸቱ 3:00 ድረስ ሰፊ ውይይት ተደርጎ ተጠናቋል፡፡ በውይይቱም የዞን እና የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የከተማ ከንቲባዎች፣ የክለብ አመራሮች፣ አሰልጣኞች፣ ቡድን መሪዎች፣ የደጋፊ ተወካዮች እና ከደቡብ ክልል የተወጣጡ በእግር ኳሱ እና እግር ኳሱ በተዘዋዋሪ የሚመለከታቸው አካላት በአጠቃላይ ከ450 በላይ ተሳታፊዎችን ተገኝተዋል፡፡ መድረኩን በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ የደቡብ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ሲሆን አቶ ገልገሎ ገዛኸኝ  (የስፖርት ሳይንስ ምሁር እና የቢሮው ስፖርት ዘርፍ ኃላፊ) ለእግር ኳሱ መቀጨጭ አንዱ መንስኤ በሆነው የስፖርታዊ ጨዋነት ጉድለቶች ላይ የተሰራ ጥናት የያዘ ሰነድ ለታዳሚው አብራርተዋል፡፡ በሰነዱ ላይ የስፖርታዊ ጨዋነት ችግሮች ተብለው በርካታ ጉዳዮች ተጠቁመዋል፡፡ የክለብ አመራሮች ላልተገባ ጥቅም መሮጥ በተለይ ዳኞችን እና ኮሚሸነሮችን በጥቅም የመደልደል፣ አሰልጣኞች ተጫዋቾችን ለፀብ ማነሳሳት፣ የቡድን መሪዎች ቡድን ከመምራት ተግባራቸው ውጪ በማይመለከታቸው ጉዳዮች በመግባት ችግር የመፍጠር፣ ተጫዋቾች በሜዳ ላይ የጠበኝነት ባህሪን ለማሳየት መነሳሳት፣ የተደራጀ የአደጋገፍ ስልት በደጋፊው እና በደጋፊዎች ማህበር ላይ ያለመታየት፣ ብሔርን እየጠሩ አሰልጣኝ እና ተጫዋች መሳደብ፣ የፀጥታ አካላት የተሰጣቸውን ኃላፊነት ከመወጣት ይልቅ ለከተማቸው ክለብ አልያም ለሚደግፉት ክለብ መወገን፣ የሚዲያ ተ

በተመድ የአሜሪካ ቋሚ መልዕክተኛ መንግሥት ለሕዝብ ፍላጎት ምላሽ እንዲሰጥ ጠየቁ

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የአሜሪካ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ኒኪ ሐሌ ሰኞ ጥቅምት 13 ቀን 2010 ባደረጉት ቆይታ፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸው ታወቀ፡፡ በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ ከሪፖርተር ለቀረበለት ጥያቄ በሰጠው ምላሽ፣ አምባሳደር ሐሌ ሕዝብ በሰላማዊ መንገድ የሚሰማውን መግለጽ፣ መንግሥትም ለሕዝብ ፍላጎት ምላሽ መስጠት እንዳለበት መጠየቃቸውን አስታውቋል፡፡ በተጨማሪም በኢትዮጵያ ሁሉንም አሳታፊ የሆነ የፖለቲካ ምኅዳር እንዲፈጠርና ገንቢ ውይይቶች እንዲካሄዱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር መነጋገራቸው ተገልጿል፡፡ አምባሳደሯ የወጣቶች ድምፅ እንዲሰማ፣ ወጣቶች መጪውን ጊዜ ብሩህ ለማድረግ ሚና እንዳላቸው ጠቁመው የአፍሪካ መሪዎችም የዜጎቻቸውን መብቶች ማክበር እንዳለባቸው ማሳሰባቸው ታውቋል፡፡ አምባሳደሯ በትዊተር አካውንታቸው ላይ እንደገለጹት፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ጋር በነበራቸው ቆይታ ስለኢትዮጵያ፣ ኢጋድና ደቡብ ሱዳን፣ እንዲሁም በኮንጎ ስላሉ ወቅታዊ ጉዳዮች መወያየታቸውን ጽፈዋል፡፡ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ቀጣይነት ባለው ኢኮኖሚያዊ ዕድገት፣ በሰላምና በመረጋጋት ላይ መነጋገራቸውን የአሜሪካ ኤምባሲ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ቀረቤታ እንዳላቸው የሚነገርላቸው ሴናተር ጀምስ ኢንሆፍ ካደረጉት ጉብኝት አንድ ሳምንት በኋላ የመጣው የአምባሳደሯ ጉብኝት፣ በአኅጉራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጓል፡፡ ከዚህ ቀደም ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ የተለያዩ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ያገኙት ሴናተር ኢንሆፍ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በሚታየው የፖለቲካ ውጥረት ላይ መነጋገራቸው ይታወሳል፡፡ የፕሬዚዳንት ትራምፕ አስተዳደር ወደ ሥልጣን ከወጣ በኋላ በትልቅነቱ የ