Posts

በኦሮሚያ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ 30 ሰዎች ሞተዋል

Image
240 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል በኦሮሚያ ክልል በቡኖ በደሌ ዞንና በአምቦ ከተማ በአንድ ሳምንት ውስጥ 30 ሰዎች ሲሞቱ፣ 37 ያህል ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ በቡኖ በደሌ ዞን በገቺ፣ በደሌ፣ ጮራና ዴጋ ወረዳዎች ጥቅምት 12 ቀን 2010 ዓ.ም. ግጭት መቀስቀሱ የሚታወስ ሲሆን፣ በዚህ ግጭት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 20 መድረሱ ተገልጿል፡፡ በግጭቱ ምክንያት ወደ ሥፍራው አቅንተው የነበሩት የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሡ ጥላሁን ጥቅምት 17 ቀን 2010 ዓ.ም. ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ግጭቱ በተቀሰቀሰበት ወቅት የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ስለነበሩ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ሊጨምር ችሏል፡፡ በወቅቱ 14 ሰዎች መሞታቸውን፣ ከሃምሳ በላይ ቤቶች መቃጠላቸውን፣ በ14 ሰዎች ላይ ከፍተኛ የአካል ጉዳት መድረሱን፣ 1,500 መፈናቀላቸው መዘገቡ ይታወሳል፡፡ አሁን በደረሰው መረጃ መሠረት 20 ሰዎች ሲሞቱ፣ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 14 ቢሆኑም፣ የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ግን ከሦስት ሺሕ በላይ እንደሆነ አቶ ንጉሡ ገልጸዋል፡፡ አቶ ንጉሡ እንዳሉት ግጭቱ በተከሰተበት ዞን በአብዛኛው ሕይወታቸውን ያጡት የኦሮሚያ ክልል ተወላጆች ናቸው፡፡ የአማራ፣ የትግራይና የደቡብ ክልሎች ተወላጆችም ሕይወታቸውን እንዳጡ አክለዋል፡፡ የዚህ ግጭት ዋነኛ ምክንያት ምንድነው ተብሎ ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ንጉሡ፣ ‹‹በኦሮሚያ ክልል ኅብረተሰቡ ቅሬታውን በሠልፍ እንደሚገልጽ እያስተዋልን ነው፡፡ ይህም አካባቢ ሠልፍ ከሚካሄድባቸው መካከል አንዱ እንደሆነ አይተናል፡፡ ሠልፉም በሰላማዊ ሁኔታ እንደተጠናቀቀ ሰምተናል፡፡ ነገር ግን ሠልፉ ከተካሄደ በኋላ ወደ ዘረፋና ብጥብጥ ነው ያመራው፡፡ ሕዝቡ ሠልፉን በሰላም

“ቅድሚያ ለስፖርታዊ ጨዋነት” የግንዛቤ ማስጨበጫ እና ውይይት መድረክ በሀዋሳ ተካሄደ

Image
“ቅድሚያ ለስፖርታዊ ጨዋነት” በሚል መርህ በሀዋሳ የስፖርታዊ ጨዋነት ግንዛቤ ማስጨበጫ እና ውይይት መድረክ በደቡብ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ እና በክልሉ እግርኳስ ፌድሬሽን ትብብር አርብ በኃይሌ ሪዞርት ተካሂዷል፡፡ መድረኩን ለማዘጋጀት የታሰበው ጥቅምት 17 እና 18 ቢሆንም አርብ ከጠዋት ጀምሮ እስከ ምሸቱ 3:00 ድረስ ሰፊ ውይይት ተደርጎ ተጠናቋል፡፡ በውይይቱም የዞን እና የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የከተማ ከንቲባዎች፣ የክለብ አመራሮች፣ አሰልጣኞች፣ ቡድን መሪዎች፣ የደጋፊ ተወካዮች እና ከደቡብ ክልል የተወጣጡ በእግር ኳሱ እና እግር ኳሱ በተዘዋዋሪ የሚመለከታቸው አካላት በአጠቃላይ ከ450 በላይ ተሳታፊዎችን ተገኝተዋል፡፡ መድረኩን በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ የደቡብ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ሲሆን አቶ ገልገሎ ገዛኸኝ  (የስፖርት ሳይንስ ምሁር እና የቢሮው ስፖርት ዘርፍ ኃላፊ) ለእግር ኳሱ መቀጨጭ አንዱ መንስኤ በሆነው የስፖርታዊ ጨዋነት ጉድለቶች ላይ የተሰራ ጥናት የያዘ ሰነድ ለታዳሚው አብራርተዋል፡፡ በሰነዱ ላይ የስፖርታዊ ጨዋነት ችግሮች ተብለው በርካታ ጉዳዮች ተጠቁመዋል፡፡ የክለብ አመራሮች ላልተገባ ጥቅም መሮጥ በተለይ ዳኞችን እና ኮሚሸነሮችን በጥቅም የመደልደል፣ አሰልጣኞች ተጫዋቾችን ለፀብ ማነሳሳት፣ የቡድን መሪዎች ቡድን ከመምራት ተግባራቸው ውጪ በማይመለከታቸው ጉዳዮች በመግባት ችግር የመፍጠር፣ ተጫዋቾች በሜዳ ላይ የጠበኝነት ባህሪን ለማሳየት መነሳሳት፣ የተደራጀ የአደጋገፍ ስልት በደጋፊው እና በደጋፊዎች ማህበር ላይ ያለመታየት፣ ብሔርን እየጠሩ አሰልጣኝ እና ተጫዋች መሳደብ፣ የፀጥታ አካላት የተሰጣቸውን ኃላፊነት ከመወጣት ይልቅ ለከተማቸው ክለብ አልያም ለሚደግፉት ክለብ መወገን፣ የሚዲያ ተ

በተመድ የአሜሪካ ቋሚ መልዕክተኛ መንግሥት ለሕዝብ ፍላጎት ምላሽ እንዲሰጥ ጠየቁ

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የአሜሪካ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ኒኪ ሐሌ ሰኞ ጥቅምት 13 ቀን 2010 ባደረጉት ቆይታ፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸው ታወቀ፡፡ በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ ከሪፖርተር ለቀረበለት ጥያቄ በሰጠው ምላሽ፣ አምባሳደር ሐሌ ሕዝብ በሰላማዊ መንገድ የሚሰማውን መግለጽ፣ መንግሥትም ለሕዝብ ፍላጎት ምላሽ መስጠት እንዳለበት መጠየቃቸውን አስታውቋል፡፡ በተጨማሪም በኢትዮጵያ ሁሉንም አሳታፊ የሆነ የፖለቲካ ምኅዳር እንዲፈጠርና ገንቢ ውይይቶች እንዲካሄዱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር መነጋገራቸው ተገልጿል፡፡ አምባሳደሯ የወጣቶች ድምፅ እንዲሰማ፣ ወጣቶች መጪውን ጊዜ ብሩህ ለማድረግ ሚና እንዳላቸው ጠቁመው የአፍሪካ መሪዎችም የዜጎቻቸውን መብቶች ማክበር እንዳለባቸው ማሳሰባቸው ታውቋል፡፡ አምባሳደሯ በትዊተር አካውንታቸው ላይ እንደገለጹት፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ጋር በነበራቸው ቆይታ ስለኢትዮጵያ፣ ኢጋድና ደቡብ ሱዳን፣ እንዲሁም በኮንጎ ስላሉ ወቅታዊ ጉዳዮች መወያየታቸውን ጽፈዋል፡፡ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ቀጣይነት ባለው ኢኮኖሚያዊ ዕድገት፣ በሰላምና በመረጋጋት ላይ መነጋገራቸውን የአሜሪካ ኤምባሲ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ቀረቤታ እንዳላቸው የሚነገርላቸው ሴናተር ጀምስ ኢንሆፍ ካደረጉት ጉብኝት አንድ ሳምንት በኋላ የመጣው የአምባሳደሯ ጉብኝት፣ በአኅጉራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጓል፡፡ ከዚህ ቀደም ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ የተለያዩ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ያገኙት ሴናተር ኢንሆፍ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በሚታየው የፖለቲካ ውጥረት ላይ መነጋገራቸው ይታወሳል፡፡ የፕሬዚዳንት ትራምፕ አስተዳደር ወደ ሥልጣን ከወጣ በኋላ በትልቅነቱ የ

ኢህአዴግ በህዝብ ያለውን ቅቡልነት፣ በህዝበ ውሳኔ እንዲያረጋግጥ ተጠየቀ

የሀገሪቱ የፖለቲካ ችግር ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ መምጣቱንና ለሀገሪቱ ቀጣይ ህልውናም አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱን የጠቆመው የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ (ኢራፓ)፤ ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በህዝብ ያለውን አመኔታና ቅቡልነት ህዝበ ውሳኔ በማካሄድ እንዲያረጋግጥ ጠይቋል፡፡  ፓርቲው በወቅታዊ የአቋም መግለጫው፣ የሀገሪቱን የፖለቲካ ችግሮች ከስር መሰረታቸው ሲገመግም መሰንበቱን ጠቁሞ፤ በ2007 ዓ.ም የተካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ አሸናፊነቱ የታወጀው ኢህአዴግ የመሰረተው መንግስት ላይ ውሎ ሳያድር ተቃውሞ ማየሉ፣ በሀገሪቱ ጤናማ ያልሆነ የፖለቲካ አካሄድ እንዳለ ያመላክታል ብሏል።  “በአሁኑ ወቅት ከሚታዩት ህዝባዊ ተቃውሞዎችና ግጭቶች አንጻር፣እንደ ሀገርና ህዝብ ህልውናችንን አስጠብቀን ለመሄድ አጠራጣሪ ሆኗል” ያለው ፓርቲው፤ ሁሉንም ወገኖች ያካተተ የብሄራዊ መግባባት መድረክም በአስቸኳይ መፈጠር እንዳለበት አሳስቧል፡፡   ከ2007 ምርጫ ማግስት ጀምሮ በሃገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ተቀስቅሶ እስካሁን መብረድ ያልቻለውን ተቃውሞ በቅጡ መመርመር ያሻል የሚለው ኢራፓ፤ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት በመራጮቻቸው አመኔታ በሚያጡበት ወቅት ስለሚወሰድ እርምጃ የወጣውን አዋጅ 88/1989 ዓ.ም በመጥቀስም፡- መራጩ ህዝብ በአሁኑ ወቅት በኢህአዴግ ላይ ያለውን አመኔታ ለመለካት ህዝበ ውሣኔ በአስቸኳይ እንዲካሄድ ጠይቋል፡፡ ፓርቲው ይህን ጥያቄውንም አግባብ ላለው አካል ያለመታከት እንደሚያቀርብ አስታውቋል፡፡ መንግስት ለፖለቲካ የጋራ ውይይት፣ለሃገራዊ መግባባትና ብሄራዊ እርቅ ራሱን እንዲያዘጋጅ የተለያዩ አካላት ምክር እንዲለግሱ የጠየቀው ፓርቲው፤ የኢህአዴግ አመራሮች ስልጣናቸውንና ሃላፊነታቸውን በገዛ ፍቃዳቸው በመልቀቅም ለለውጥ ተፅእኖ እየፈጠሩ መሆኑን በአድናቆት እን

St. George, Hawassa women’s teams in the buildup

Image
Photo St. George appeared impressed by the appointment of Selam Zeray to Ethiopian U-20 women’s national team head coach position after the management gave a green light for the signing of four players including former Lucy midfielder Tutu Belay to her second stint with the club. Knockout holders Hawassa Ketema is also in a signing spree following the parting of seven senior players. In high spirit to emerge strong title contender in the newly formed Women’s league season, St. George brings in four players to its squad. The renowned mid fielder Tutu Belay is back to St. George after a single unsuccessful season with Addis Ababa Ketema while Semira Kemal returned to football after four years absence following motherhood. Former Ethiopia NegedBank mid fielder Bezawit Tesfaye and defender Etaferahu Adrse are the other two players that joined St. George. “Selam is smart for signing those players for her team that does have experience and team spirit” suggested a former footballer. I

Mulualem to Hawassa while Mohammed joins Fasil

Image
Hawassa Ketema signed former renowned mid fielder Mulualem Regasa after two months trial while much travelled striker Mohammed Naser joined Fasil Ketema. Photo Though the 37 year-old former St. George, Sebeta Ketema and Ethiopia Medin playmaker had been far from Football for the past two seasons, Hawassa gave him a two months trial period in which he impressed the management and handed him a one year contract worth 500,000 Birr. Famous for his inch perfect long passes and vision both at St. George and Ethiopian national team, Mulualem’s return to premier league football took many by surprise taking into consideration his age and 21 years in league football. “When it comes to creative football I am sure he could perform by far better than the current active players and definitely to give an extra fire power to Hawassa. Cap in hand for Wubetu Abate’s decision” remarked a former player. “It doesn’t show Mulualem’s extraordinary talent but rather a classic showcase about the shockin

Chester physio helps to change bed rest culture in Ethiopia

Image
When senior physiotherapist Nicola Jarman of  Chester  travelled to Ethiopia earlier this year she had no idea how challenging, yet inspiring and heart-warming it would be. Having been picked as one of two physios to represent the North West Orthopaedic Trauma Alliance for Africa (NOTAA) she arrived in Hawassa, via Istanbul and Addis Ababa, filled with enthusiasm and excitement. Nicola joined forces with Laura Knowles from St Helens and Knowsley NHS Trust and Rebekah Laurenson from Perth, Australia, as a specialist team within a nine-strong specialist orthopaedic team sent to Hawassa Hospital to share best practice and ideas. Nicola, who has worked at the  Countess of Chester Hospital  for four years, said: “At first nobody working at the hospital really knew what the role of a physiotherapist should be. They would tell patients to stay in bed and just rest after surgery because they hadn’t been taught when it was best to get people moving again.” Nicola tends to a patie