ከአንድ ሚሊዮን ህዝብ በላይ በተገኘበት በሃዋሳው ጉዱማሌ የፍቼ ጫምባላላ በዓል እየተከበረ ነው

 የፍቼ ጫምባላላ በዓል በሀዋሳ ከተማ ጉዱማሌ እየተከበረ ነው። 
በበዓሉ ላይ የደቡብ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ፣ የኦሮሚያ ክልል  ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች  በተገኙበት በሀዋሳ ጉዱማሌ እየተከበረ ነው።
በዓሉን ለማክበር ከሲዳማ ዞን 32 ወረዳዎች፣ ከደቡብ  ብሄሮች፣ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ተወካዮች ተሳትፈውበታል።
የሲዳማ ሕዝብ የዘመን መለወጫ የሆነው በዓል  በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት/ዩኔስኮ/ በዓለም ቅርስነት ከተመዘገበ ሦስት ዓመታትን  አስቆጥሯል።
በበዓሉ ላይ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚገመቱ ተሳታፊዎች መገኘታቸውም ተጠቅሷል።

Comments

Popular posts from this blog

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ