ህገመንግሰታዊ መብታችን ይከበር በሚል መሪ ቃል በሀዋሳ ሰለማዊ ሰልፍ እየተደረገ ነው

በሰለማዊ ሰልፉ ከሲዳማ 36 ወረዳዎች እና ከተማ መስተዳድሮች የተውጣጡ እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች የተሳተፉበት ነው።
ሰለማዊ ሰልፈኞቹ “ህገ መንግስቱ ይከበር ! የሲዳማ የክልልነት ጥያቄ መልስ ይሰጠው! የሪፈረንደም ቀን ይወሰን !” የሚሉና መሰል መፈክሮችን እያሰሙ ነው።
መነሻውን ከሀዋሳ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ያደረገው ሰላማዊ ሰልፍ በሀዋሳ ዓለምአቀፍ ስታዲዮም መዳረሻውን በማድረግ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ደኢህዴን/ ከወራት በፊት ባደረገው በ10ኛ መደበኛ ጉባኤው የሲዳማ ብሔር በክልልነት የመደራጀት ጥያቄ ተቀብሎ ለህዝበ ውሳኔ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መምራቱ ይታወሳል።
ebc

Comments

Popular posts from this blog

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ