ህፃናትን በበጉዲፈቻ ወደ ውጭ አገር መላክ የሚፈቅደው አንቀጽ ከኢትዮጵያ ቤተሰብ ሕግ እንዲሠረዝ ተወሰነ

የውጭ አገር ጉዲፈቻ የተፈጥሮ ቤተሰብ ፍቅርና እንክብካቤን ሙሉ በሙሉ የማይተካና ከዚህ ቀደም በጉዲፈቻ ወደ ውጭ አገራት የሄዱ ህፃናት ላይ የማንነት ቀውስ በማስከተሉ፣ ይህን አሠራር የሚፈቅደው የሕግ ድንጋጌ ከቤተሰብ ሕጉ እንዲሠረዝ መንግሥት ወሰነ።
በዚህም መሠረት የቤተሰብ ሕጉ ላይ ማሻሻያ የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ ዛሬ ለፓርላማ ቀርቦ ለዝርዝር እይታ ተመርቷል ። የውጭ ጉዲፈቻን በሚፈቅደው ሕግ አማካይነት ተጀምረው በፍርድ ቤት ሂደት ላይ የሚገኙ እንዲቀጥሉ ማሻሻያው ይፈቅዳል።
በሌላ በኩል የመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ የተለያዩ ማሻሻያዎችን አካቶ ለፓርላማ የቀረበ ሲሆን፣ ለእናቶች ከወሊድ በኋላ ይፈቀድ የነበረው የሁለት ወር ዕረፍት ሦስት ወር እንዲሆን፣ በድምሩ እናቶች ለቅድመና ድህረ ወሊድ የአራት ወር እረፍት እንዲያገኙ በረቂቅ ሕጉ ተካቶ ቀርቧል።

Comments

Popular posts from this blog

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ