በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ቅናሽ ተደረገ

የንግድ ሚኒስቴር በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ቅናሽ ማድረጉን አስታወቋል ።
የዋጋ ቅናሽ ማሰተካከያ የተደረገው የነዳጅ ምርቶች የአለም ገበያ ዋጋ እየቀነሰ መምጣቱን መነሻ በማድረግ መሆኑን ነው ሚኒስቴሩ ለፋና ብሮድካስቲነግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ ያስታወቀው ።
በዚህም መሰረት ከነገ ጥር 23 እስከ የካቲት 30፣ ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ የነደጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋን ይፋ አድርጓል ።
በዋጋ ክለሳውም ቤንዚን ኢታኖል ድብልቅ በሊትር 17 ብር ከ20 ሳንቲም ፣ ነጭ ናፍታ 16 ብር ከ10 ሳንቲም ፣ ኬሮሲን 14 ብር ከ42 ሳንቲም ፣ ቀላል ጥቁር ናፍጣ 13 ብር ከ91 ሳንቲም ፣ እንደዚሁም ከባድ ጥቁር ናፍታ 13 ብር ከ23 ሳንቲም ሲሆን፥ የአውሮፕላን ነዳጅ ደግሞ 15 ብር ከ21 ሳንቲም በሊትር የሚሸጥ ይሆናል ።
ሚኒስቴሩ የነዳጅ ምርቶቹን ዋጋ በዝርዝር በነገው እለት በጋዜጣ የሚያወጣ መሆኑንና በሁሉም የሃገሪቱ ክፍል ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑንም አስታውቋል ።

Comments

Popular posts from this blog

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ