ዶ/ር ቤታና ሆጤሶ በሲዳማ ታሪክ ላይ ያደረጉት ወይይት Get link Facebook X Pinterest Email Other Apps September 30, 2014 ዶ/ር ቤታና ሆጤሶ በሲዳማ ታሪክ ላይ ያደረጉት ወይይት፦ Dr Betana Hoxesso Sidama Liberation Front Vice Chair Person discuss about Sidama history Get link Facebook X Pinterest Email Other Apps Comments
የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት September 01, 2019 የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው... Read more
የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች! February 21, 2022 ከሰሞኑ አንዳንድ የስራ ሀላፊዎች የቻርተር አውሮፕላን በረራዎችን ደጋግመው ሲጠቀሙ ተመልክተናል። ታድያ እነዚህ በአንድ ጉዞ ብቻ የመቶ ሺህ ብሮችን ወጪ የሚጠይቁ በረራዎች የተካሄዱት የኢትዮጵያ አየር መንገድ መደበኛ በረራ ጠፍቶ ወይስ በምን አግባብ ይሆን? በግሌ ለማየት እንደሞከርኩት በነዚህ ቀናት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎች ነበሩ። ለምሳሌ ባለፈው አርብ የሲዳማ ክልል ፕሬዝደንት የሚድሮክን King Air 360 ቻርተር አውሮፕላን በተጠቀሙበት እለት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ET228 ከአዲስ አበባ ወደ ጅግጅጋ በረራ ነበረው፣ ሌሎቹም እንዲሁ። እርግጥ ነው እንደ ቡህታን ንጉስ ያሉ ቢሊየነሮች አይደለም የቻርተር በረራ የራሳቸው ግዙፍ አውሮፕላን አላቸው። ነገር ግን ተጠያቂነት ባለባቸው ሀገራት ከህዝብ በሚሰበሰብ ገንዘብ እንዲህ አይነት አሰራር አይታሰብም። በአንድ ወቅት የአሜሪካው ሴናተር ቴድ ክሩዝ በመንገደኛ አውሮፕላን ከህዝብ ጋር ተሳፍረው ሳለ ያጋጠማቸውን ሰምታችሁ/አንብባችሁ ይሆናል። ጦርነት፣ ድርቅ እንዲሁም ሌሎች ውስጣዊ እና ውጫዊ ምክንያቶች ከፍተኛ ጫና ሀገር ላይ እያደረሱ ባሉበት ወቅት እንዲህ አይነት ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ ጉዞዎች ተገቢ ናቸው ብላችሁ ታስባላችሁ? ኤሊያስ መሰረት Read more
በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ December 14, 2024 በባህርዳር ከተማ ተገኝተው ልምዱን ያካፈሉት “የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የፍትህ ቢሮ ም/ሀላፊና የህግ ጉዳዮች ዘርፍ ሀላፊ ክብርት ወ/ሮ አሽሌ ዳንኤል ሲሆኑ:- እንደ ሲዳማ ብሔር ይህ ቱባ ባህል የከበረ ባህል ሲሆን ዕድሜ ጠገብና እጅግ የሚያኮራ እንዲሁም ለዕርቅና ለሰላም ግንባታ ትልቅ ሚና ያለው ባህል ብለዋል። "አፊኒ" ትልቅ የሀገር እሴት መሆኑንና ይህንንም ባህላዊ የዳኝነት ስርአትን የሚደግፍ የማህበረሰብ ፍትህ አገልግሎትን ለማጠናከር የሚረዳ አዋጅ በሲዳማ ክልል ምክር ቤቱ እንዳፀደቀ ገልፀዋል:: በመድረኩ የኢፌዲሪ ፍትህ ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኤርሚያስ የማነብርሐን, የክልሉ ም/ቤት አፈጉባኤ ክብርት ፋንቱ ተስፋዬና የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አለምአንተ አግደዉ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል:: የማህበረስብ አቀፍ ፍትህ አገልግሎት ሚናን አስመልክቶ የሲዳማ ብሔር "አፊኒ" ባህላዊ ዳኝነት ስርዓትና ተሞክሮን በተመለከተ ህብረተሰቡ ዘመናዊ የዳኝነት ስርዓትን በማይቃረን መልኩ ሳይጉላላና ለአላስፈላጊ ወጪ ሳይዳረግ ፍትህ እንዲያገኝ በማሰብ እየተሰራ ያለ መሆኑ ተገልፆአል:: በአማራ ክልል ባህርዳር ከተማ የተዘጋጀው መድረክ ላይ ክልሉ የራሱን የረቂቅ ሞዴል ህግ እንዲሁም ሌሎች የጥናት ጽሁፎችና የኦሮሚያ ክልል ልምድም ቀርቦ በሀገር ሽማግሌዎች: የሐይማኖት አባቶችና ምሁራን ሠፊ ውይይት ተደርጎአል። የባህል ፍርድ ቤቶችን ስለማቋቋምና እዉቅና ስለመስጠት፣ የባህላዊ ግጭት መፍቻ ዘዴዎች ዳሰሳ መደረጉ ስርአቱን ለማጠንከር ማህበረሰዋዊና ብሎም ሀገራዊ ሰላምን አብሮነትን የሚያጠነክር መሆኑም ተነስቶ ከሲዳማና ከኦሮሚያ ክልል ለቀረቡ ልምዶች ላቅ ያለ ምስጋና ተችሮአል:: FastMereja.com Read more
Comments
Post a Comment