ኢትዮጵያን ጨምሮ በአለማችን ከ800 ሚ. በላይ ህዝብ የምግብ እጥረት ተጠቂ ነው ተባለ
ኢትዮጵያ ችግሩ ከተስፋፋባቸው አገራት አንዷ ናት ተብሏል

የአለም የምግብና የእርሻ ድርጅት እንዳለው፣ ምንም እንኳን በአለማችን በአሁኑ ወቅት ከሚያስፈልገው የምግብ እህል ከሁለት እጥፍ በላይ ማምረት ቢቻልም፣ ምርቱን ለተመጋቢዎች በማድረስ ረገድ ክፍተቶች በመኖራቸው የምግብ እጥረት ችግሩ ሊቀረፍ አልቻለም፡፡ ምርታማነት ቢያድግም የተመረተውን የምግብ እህል ለሸማቾችና የችግር ተጋላጭ ለሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ማድረስ ካልተቻለ፣ የምግብ እጥረቱ እንደማይቀረፍ የገለጸው ድርጅቱ፣ ለዚህም ሴፍቲ ኔትና ሌሎች የማህበራዊ ዋስትና አሰራሮችን ማጠናከር እንደሚገባ አስታውቋል፡፡
ከሚሊኒየሙ የልማት ግቦች አንዱ በታዳጊ አገራት የምግብ እጥረት የሚያጋጥማቸውን ዜጎች ቁጥር እስከ 2015 ድረስ በግማሽ መቀነስ መሆኑን ያስታወሰው ዘገባው፤ የተመድ ሪፖርትም ግቡን ለማሳካት እንደሚቻል አመላካች ውጤቶች እየተመዘገቡ እንደሚገኙ ማስታወቁን ጠቁሟል፡፡ ይሄም ሆኖ ግን፣ ከሰሃራ በታች በሚገኙ አገራትና በመካከለኛው ምስራቅ የሚከሰቱ Yተፈጥሮ አደጋዎችና ግጭቶች፣ የአካባቢው አገራት ግቡን ለማሳካት የሚደርጉትን እንቅስቃሴ እያደናቀፉት እንደሚገኙ ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡
ምንጭ፦ ኣዲስ ኣድማስ ጋዜጣ
Comments
Post a Comment