ከ14 አመት በታች ብሔራዊ ቡድን ለአለም ዋንጫ ጨዋታ ወደ አሜሪካ ተጓዘ

አዲስ አበባ፣ ሀምሌ 12፣2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) የኢትዮጵያ ከ14 አመት በታች ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ለአለም ዋንጫ ጨዋታ ወደ አሜሪካ ተጓዘ።
በፓሽን የስፖርት አካዳሚ ላለፉት አራት ወራት በእግር ኳስ የሰለጠኑ ታዳጊዎች በቺካጎ ከሐምሌ 12 -19 /2014 በሚደረገው የአለም ዋንጫ ውድድር ለማካፈል ወደ ስፍራው አቅንተዋል።
ኢትዮጵያ እና ጋና ከአፍሪካ ጨምሮ አስራ አንድ አገራት በሚሳተፉበት ውድድር አሰልጣኝ አሰግድ ተስፈዬ እና 18 አባላት የያዘው የኢትዮጵያ ቡድን ወደ አሜሪካ ተጉዟል።

Comments

Popular posts from this blog

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

Reclaiming Truth: A Rebuttal to the Misrepresentation of the Sidama People’s Struggle and Cultural Legacy