ሲዳማ ቡና ከአርባ ምንጭ ከነማ ባዶ ለባዶ ተለያዩ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 23 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) በ22ተኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና እና ንግድ ባንክ ድል ቀንቷቸዋል።
ንግድ ናንክ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ነው ኢትዮጵያ መድህንን 2 ለ 0 የረታው።
በክልል ከተሞች ዳሸን ቢራ ከወላይታ ዲቻ ፣  አርባ ምንጭ ከነማ ከሲዳማ ቡና በተመሳሳይ 0 ለ 0 ሲለያዩ ፤ ሙገር ሲሚንቶ በመብራት ሃይል 2 ለ 1 ተሸንፏል።
በሌላ ጨዋታ ወደ ሀረር ያቀናው ኢትዮጵያ ቡና ሀረር ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል።
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ደደቢት ግጥሚያ 3 ለ 3 በሆነ ውጤት ተጠናቋል።

Comments

Popular posts from this blog

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ