አንድነት ለዲሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ከመድረክ አባልነት በጊዚያዊነት ታገደ፤ የሲዳማ አርነት ንቅናቄን በአዲስ አባልነት ተቀበለ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣  2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ትናንት 9ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዷል፡፡
አንድነት ለዲሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ከመድረክ አባል ፓርቲነት በጊዜያዊነት እንዲታገድ ጉባኤው መወሰኑንም የመድረክ አመራሮች አስታውቀዋል፡፡
የመድረክ ሊቀመንበር ዶክተር መረራ ጉዲና እንደተናሩት የአንድነት ፓርቲ አመራሮች የመድረክን መግባቢ ሰነድ በሚጻረር መልኩ የሰጡትን መግለጫ በይፋ እንዲያስተባብሉ ቢጠየቁም ባለማስተካከላቸው አንድነት በጊዜያዊነት ከመድረክ አባል ፓርቲነት ታግዶ እንዲቆይ በጉባኤው ተላልፏል።
የአንድነት ለዲሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ፕሬዝዳንት ኢንጅነር ግዛቸው ሽፈራው በበኩላቸው የመድረክ ውሳኔ ትክክል አይደለም ብለዋል፡፡
አንድነት የሚያስተባብለው ነገር የለም ብለዋል።
እንድም የሰጠነው አስተያየት የለም ያሉት ፕሬዚዳንቱ፥ እንደ ተቋም መድረክን ገምግመን ሰጥተናል፤  እገዳው ለምን እንደሆነ አልገባንም ብለው ለኢሬቴድ ገልጸዋል።
ጉባኤው የሲዳማ አርነት ንቅናቄን  በአዲስ አባልነት ተቀበሏል።

Comments

Popular posts from this blog

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ