ጥቂት የሲዳማ የእግር ኳስ ክለቦች ተጨዋቾችን የያዘው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ብድን በቻን ውድድር ያለምንም ግብ ተሰናበተ

አዲስ አበባ፣ ጥር 14 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ባለው 3ኛው የቻን አፍሪካ እግር ኳስ ውድድር ተሳታፊ የነበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ፥ የምድቡን የመጨረሻ ጨዋታ ትናንት ምሽት 2 ሰዓት ላይ ከጋና አቻው ጋር አድርጎ 1 ለ 0 ተሸንፏል።
ዋሊያዎቹ ምንም ጎል ሳያስቆጥሩ በአራት የጎል እዳ ከምድቡ ተሰናብተዋል።
ጋናዎች የምድብ ሶስት መሪ ያደረጋቸውን ሶስት ነጥብ ያስመዘገቡት በ76ኛው ደቂቃ ያገኙትን ፍፁም ቅጣት ምት ኩዋቢ አዱሴ ወደ ጎል በመቀየሩ ነው፡፡
በምድቡ ፥ ሊቢያ ኮንጎን በማሸነፍ  ጋናን ተከትላ ወደ ቀጣዩ ዙር የግማሽ ፍፃሜ ተቀላቅላለች፡፡

Comments

Popular posts from this blog

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ