የሲዳማ ዞን መንግስት የካቢኔ ሽግሽግ _ የቀድሞ የዞኑ የድርጅት ፖለቲካ ሀላፊ የዞኑ ዋና ኣስተዳደር

የሲዳማ ዞን መንግስት የካቢኔ ሽግሽግ ኣድርጓል። የቀድሞ  የዞኑ ዋና  ኣስተዳደር ኣቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ወደ ደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊነት የተዛወሩ ሲሆን፤ በእሳቸው ቦታ የቀድሞ የዞኑ ድርጅት ፖለቲካ ሃላፊ ካላ ኣክልሉ ኣደላ የዞኑ ዋና ኣስተዳደር ሆነዋል። በተጨማሪም በዞኑ ፋይናንስ መምሪያ በዋና ሃላፊ በመሆን ሲያገለግሉ  የቆዩት ኣቶ  በቀለ ታፎ ወደ ስቪል ስርቪስ መምሪያ  ሃላፊነት ተዛውረዋል።

በተመሳሳይ ዜና በሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደርም የካቢኔ ሽግሽግ የተደረገ ሲሆን፤ የከተማው ፍይናንስ መምሪያ  ኣዲስ ሃላፊ ተሹሞለታል።

በዞኑ ስለተላሄደው የካቢኔ ሽግሽግ እና በሽግሽጉ ዙሪያ የተሰበሰበ የህዝብ ኣስተያየት እንደደረሰን ለክቡራን ኣንባብያን እንደምናቀርብ መግለጽ እንወዳለን ወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ

  

Comments

Popular posts from this blog

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ