አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ወላሳ - የትምህርት ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 27 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተለያዩ የመንግስት ሚኒስትሮችን እና የስራ ሃላፊዎችን ሹመት አጸደቀ።
ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሰላኝ የቀረቡ እጩዎችን ሹመት በ1 ድምጸ ተዓቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል።
በዚህም መሰረት አቶ ደመቀ መኮንን - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር
አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ወላሳ - የትምህርት ሚኒስትር
አቶ ሬድዋን ሁሴን ራህመቶ-  የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሚኒስትር
አቶ አህመድ አብተው አስፋው - የኢንዱስትሪ ሚኒስትር
አቶ ወርቅነህ ገበየሁ ነገዎ - የትራንስፖርት ሚኒስትር
ወይዘሮ ሮማን ገብረስላሴ መሸሻ - በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር
ወይዘሮ ደሚቱ ሃንቢሳ ቦንሳ - የሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ሚኒስትር
አቶ ጌታቸው አምባዬ በለው - የፍትህ ሚኒስትር
አቶ በከር ሻሌ ዱሌ - የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር
አቶ በለጠ ታፈረ ደስታ - የአካባቢ ጥበቃና የደን ሚኒስትር
አቶ መኮንን ማንያዘዋል እንደሻው - የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር በመሆን የተሾሙ ሲሆን ፥ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ተገኔ ጌታነህ አማካኝነት ቃለ መሃላቸውን ፈጽመዋል።

Comments

Popular posts from this blog

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ