በሲዳማ ዞን ከ186ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት የበጎ ፈቃድ ፕሮግራም በይፋ ተጀመረ፡፡

photo http://www.flickr.com/photos/espsol/sets/72157632677473483/
አዋሳ ሐምሌ 11/2005 በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞን ከ186ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራም ትናንት ተጀመረ ። የወጣቶችን የስራ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት እንዲጠናከር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የክልሉ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ጥሪ አቀረቡ፡፡ የፕሮግራሙ መጀመር ምክንያት በማድረግ በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ ትናንት በተዘጋጀው መድረክ ላይ የዞኑ ሴቶች፣ ወጣቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ኃለፊ ውይዜሮ ሻሎ ሮርሳ እንደገለጹት የዞኑ ወጣቶች ባለፉት አራት ዓመታት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደራጀ መንገድ በመሰማራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባሮችን ሲያከናዉኑ ቆይተዋል ። የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን ወጣቶቹ ጉልበታቸውን፣ እውቀታቸውን ለአካባቢው ልማት በማዋል መልካም ተግባሮችን ከማከናወናቸዉም ሌላ ከማህበረሰቡ የተለያዩ እሴቶችን የቀስሙበት እንደነበር አስታዉቀዋል ። በዘንድሮም ክረምት ከዞኑ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ከወጣት አደረጃጀቶች ጋር በመተባበር እራሳቸውንና ህብረተሰቡን ጠቅመው የዞኑን ልማት በሚያፋጥኑ የልማት ተግባሮች ለመሰማራት እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ወይዜሮ ሻሎ አብራርቷል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢህዴን/ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አክልሉ አዱሎ በበኩላቸው የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ በከተማው ከተጀመረ ወዲህ ወጣቶች ለልማት ያላቸዉ ተነሳሽነትና ፍላጎት እየጨመረ መጥቷል ብለዋል፡፡ ወጣቶቹ በቆይታቸዉ የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት ፣ የአካባቢ ጥበቃ፣ የጤና፣ የአካባቢ ፅዳትና ውበት፣ የትራፊክ ደህንነት፣ አረጋውያንና ወላጆቻቸውን ያጡ ህፃናት መደገፍ፣ ደም ልገሳን ጨምሮ በአስራ ሶስት ዓይነት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መስኮች ይሰማራሉ ። የደቡብ ክልል ሴቶች ወጣቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት መስቀለ በፕሮግራሙ ላይ ባደረጉት ንግግር የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ዜጎች በተለይ ወጣቶች ሁለንተናዊ አቅማቸውን ለማህበረሰብና ለአካባቢው ደህንነትና ልማት በነጻ የሚያውሉበት የተቀደሰ ተግባር ነው ብለዋል፡፡ የዞኑ ወጣቶች ቀደም ሲልም የእረፍት ጊዜያቸውን በአልባሌ ቦታ ከማዋል ተቆጥበው ልማት የሚያጠናክሩና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ተግባራት ሲያከናወን መቆየታቸውን አመልከተዋል፡፡ በዚህም በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን አመልከተው ዘንድሮም በተመረጡና ፋይዳ ባላቸው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በክልል ደረጃ ከ1ሚሊዮን በላይ ወጣቶች በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ሙሉ ተሳታፊ በመሆን ካለፉት ዓመታት የተሻለ ዉጥት እንደሚያስመዘገቡ እምነታቸዉን ገልጠዋል ፡፡ ወጣቶቹ በዚህ ስራ ያሳዩትን ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት ለማጠናከር በየደረጃ የሚገኙ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የነቃ ተሳትፎና ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው ኃላፊዋ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ፕሮግራሙ በይፋ ስጀመር ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለዕረፍት የተመለሱና በዞኑ ባሉ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ በርካታ ወጣቶች የተሳተፉ ሲሆን በዕለቱም ከ20ሺህ የሚበልጡ ችግኞች ተከላም ተከናውነዋል፡፡
http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=9838&K=1

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር