ሰሞኑን በሸቤዲኖ ወረዳ በላኮ ከተማ በተነሳው እሳት ግምቱ ሁለት ሚሊዮን የሚገመት ንብረት መውደሙ ተነግሯል

ከምሽቱ ኣምስት ሰዓት ኣካባቢ ከኣንድ መኖሪያ ቤት ተነሳ የተባለው እሳት በኣካባቢው የነበሩት ወደ 12 የሚሆኑ የንግድ ቤቶችን ያቃጠለ ሲሆን ከተቃጠሉት የንግድ ቤቶች መካከል የምግብ ቤቶች፤ የሸቀጣሸቀጥ መደብሮች፤ የመድሃኒት ቤት፤ የህንጻ መሳሪያ መሸጫን የመሳሰሉት ይገኙበታል።
ቃጠሎው ያወደማቸውን ቤቶች ተዘዋውረው የጎበኙት የዞኑ ካፍተኛ ባለስልጣናት ንብረታቸውን በእሳት ላጡ ለከተማዋ ነዋሪዎች መንግስት ድጋፍ እንደሚያደርግ መናገራቸው ተሰምቷል።

Comments

Popular posts from this blog

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ