የሃዋሳ ከተማን የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ልማት ለማፋጠን የነዋሪዎችና የልማት አጋሮች ተሣትፎ ወሣኝ ነው

ሃዋሣ, የካቲት 14 ቀን 2003 (ሃዋሳ) - የሃዋሳ ከተማን የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ልማት ለማጥፋጠን በሚደረገው ጥረት የነዋሪዎችና የልማት በአጋሮች ድጋፋቸውን አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የከተማው አስተዳደር ከንቲባ አስታወቁ፡፡

የሃዋሣ 50ኛ ዓመትና ሁለተኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ቀን በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ ከ80 በላይ ግለሰቦችና ድርጅቶች የከተማው አስተዳደር ትናንት የምስጋና የምስክር ወረቀት ሰጥቷል፡፡

በዚሁ ወቅት ከንቲባው አቶ ሽብቁ ማጋኔ እንደገለፁት በዓሉ በፈጠረው ምቹ ሁኔታ የከተማውን ሁለንተናዊ ገጽታ ለማስተዋወቅ ተችሏል፡፡

ከ80 በላይ የኢትዮጵያ ከተሞችና ከ40 በላይ ድርጅቶች የተሣተፉበትን ይህንኑ በዓል ተከትሎ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ፍሰት በእጅጉ መጨመሩን ገልፀዋል፡፡

በአሉ ሃዋሳ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ እንዲሁም የፈጣን ልማት፣ የእድገትና የአንድነት ተምሣሌት መሆኗን ማስመስከር የተቻለበት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ለዚህም ስኬት መላው ነዋሪ ህዝብና የልማት አጋሮች ያደረጉት ተሣትፎ ከፍተኛ እንደነበር ገልፀዋል፡፡

ለበአሉ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ያደረጉ ከ80 በላይ ግለሰቦችና ድርጅቶች ትናንት ምሽት በተዘጋጀው ኘሮግራም ላይ ከከተማው ከንቲባ ከአቶ ሽብቁ ማጋኔ እጅ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል፡፡

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር