በሃዋሳ ከተማ በግጭት አፈታትና ሰላም ላይ የሚመክር አህጉራዊ አውደ ጥናት ተጀመረ

ሃዋሳ, የካቲት 14 ቀን 2003 (ሃዋሳ) - በምስራቅ አፍሪካ በየነ መንግስታት አባል ሀገሮች ኢጋድ ድንበር ተሻጋሪ አካባቢ በሚኖሩ ህብረተሰብ መካከል የግጭት አፈታትና ሰላም ላይ ምርጥ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ የተዘጋጀ አውደ ጥናት ዛሬ በሃዋሳ ከተማ ተጀመረ ።

በኢጋድ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ ተቋም ከጀርመን መንግስት ጋር በመተባበር ለሦስት ቀናት በተዘጋጀ አውደ ጥናት ላይ ከኢትዮጵያ ፣ከኬኒያ ፣ ከሶማሌያ፣ከጅብቲ፣ከሱዳንና ኡጋንዳ ድንበር ተሻጋሪ አካባቢ የሚኖሩ የህብረተሰብ ተወካዮች መሳታፋቸውን የተቋሙ ህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ኦፊሰር ሚስስ ትእግስት ሀይሉ ገልፀዋል ።

ተሳታፊዎቹ በቆይታቸው በግጭት አፈታት ፣በሠላም ፣በልማትና ሌሎች የጋራ ስምምነትና ጥቅሞች ላይ የየአካባቢያቸውን ምርጥ ተሞክሮ በተናጥልና በቡድን በማቅረብ የልምድ ልውውጥ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል ።

የምርጥ ተሞክሮና የልምድ ልውውጥ መድረኩ በፊልምና በተዘጋጁ የሬዲዮ ድራማዎችና የእርስ በርስ ባህላዊ ግንኙነቶች ላይ በተደገፈ ፕሮግራም የሚካሄድ መሆኑን ገልጠዋል ።

አውደ ጥናቱን በንግግር የከፈቱት የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ናቸው ።

በአውደ ጥናቱ ላይ የየሀገሪቱ መንግስታትና የመስተዳድር ተወካዮች አጋርና መንግስታዊ ያልሆኑ ደርጅቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳተፈዋል ።

Comments

Popular posts from this blog

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

በሲዳማ ብሔር በሰፊው የሚታወቀው የ"አፊኒ" ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትና የአዋጅ ረቂቅ ተሞክሮ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ቀረበ