Posts

በሲዳማ ዞን አርቤጐና ወረዳ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማትን መሰረት ያደረጉ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የወረዳው ግብርና ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በሲዳማ ዞን አርቤጐና ወረዳ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማትን መሰረት ያደረጉ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የወረዳው ግብርና ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሽመልስ ሃጥሶ እንደገለፁት ዘንድሮ በወረዳው ውስጥ በሚገኙ ሁሉም ቀበሌዎች 38 የንኡስ ተፋሰሶችን በመለየት የተለያዩ ተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች በመሰራት ላይ ይገኛሉ፡፡ ወረዳው ያለውን ከፍተኛ የውሃ ሀብት ከግምት በማስገባት ጽህፈት ቤቱ በተያዘነው የበጀት አመት 23ዐ ሄክታር መሬት በተለያዩ የውሃ አማራጮች ለማልማት ግብ መጣሉን ገልፀዋል፡፡በእስከ አሁኑ ከ26 ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን በመጠቆም፡፡ አምዛዬ አዳነ ከበንሳ ቅርንጫፍ እንደዘገበው ፡፡ ፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/6MegTextN204.html   

በሲዳማ ዞን ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ህጋዊ ነጋዴዎችን በብዛትና በጥራት ማፍራት መቻሉን የዞኑ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ አስታወቀ :

በሲዳማ ዞን ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ህጋዊ ነጋዴዎችን በብዛትና በጥራት ማፍራት መቻሉን የዞኑ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡መምሪያው ከአንድ ሺህ በላይ ለሚሆኑ ነጋዴዎች የንግድ ፈቃድ ሰጥቶ ወደ ስራ ማስማራቱንም ጨምሮ ገልጿል፡፡ በዞኑ 19 ወረዳዎችና 2 የከተማ አስተዳደሮች 1 ሺህ 4 መቶ 44 የንግድ ፈቃድ ምዝገባ ለማካሄድ ታቅዶ ከዕቅድ በላይ 1 ሺህ 6 መቶ 12 የንግድ ምዝገባ ማከናወን መቻሉን በመምሪያ የንግድ ማስፋፊያ ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ሲኮራ ኤቢሶ ገልፀዋል፡፡በበጀት አመቱ 1ዐ ሺህ 214 የሚሆኑ የንግድ ተቋሟት የምዝገባና የንግደ ፈቃድ አገልግሎት ማግኘታቸውን ገልፀው በዚህም 1 ሚሊዮን 52 ሺህ ብር ገቢ መገኘቱን አስረድተዋል፡፡ሪፖርተራችን ካሳ ጀንቦላ ከበንሳ ቅርንጫፋችን እንደዘገበው ፡፡ ፡፡

በይርጋለም ከተማ በትምህርቱ ዘርፍ የጐልማሶች ትምህርት ውጤት እያስገኘ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ገለፁ :

Image
በይርጋለም ከተማ በትምህርቱ ዘርፍ የጐልማሶች ትምህርት ውጤት እያስገኘ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ገለፁ፡፡የይርጋለም ከተማ ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ተክለስላሴ ዌኬሬ እንዳሉት ሀገሪቱ የተያያዘችውን የትራንስፎርሜሽን እቅድ ለማሣካት የሚቻለው የምክር ቤት አባላት በግንባር ቀደምትነት ተሳታፊ ሲሆኑ ነው ብለዋል፡፡ የከተማው አስተዳደር ከንቲባ አቶ ወንድወሰን ቦልካ በ6 ወራቱ የስራ ክንውን መከላከልን መሰረት ያደረገው የጤና ፖሊሲ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልጿል ፡፡በተለይም በከተማ የጤና ኤክስቴንሽን ረገድ፡፡በትምህርት ዘርፍ የጐልማሶች ትምህርትን ለማጠናከር በተደረገው ጥረትም ውጤታማ ተግባር መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ምክር ቤቱ የ3 ካቢኔ አባላትን ሹመት ያፀደቀ ሲሆን በቀጣይም ለሚሰሩ ተግባራት አቅጣጫ በማስቀመጥ መጠናቀቁን የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል፡፡ ፡፡

በሀዋሣ ከተማ በሳምንቱ ከነበረው የነጭ ጤፍ የገበያ ውሎ በሀላባ ከተማ የ2ዐዐ ብር ቅናሽ መስተዋሉን የክልሉ ግብይትና ህብረት ስራ ቢሮ በላከልን መረጃ አመለከተ ::

Image
በሀዋሣ ከተማ በሳምንቱ ከነበረው የነጭ ጤፍ የገበያ ውሎ በሀላባ ከተማ የ2ዐዐ ብር ቅናሽ መስተዋሉን የክልሉ ግብይትና ህብረት ስራ ቢሮ በላከልን መረጃ አመለከተ፡፡በሀላባ ከተማ 1 ኪሎ በርበሬ 42.5ዐ ሳንቲም ዋጋ ሲሸጥ በሀዋሣ ከተማ የ14 ብር ጭማሪ አሳይቷል ፡፡በዛሬው የገበያ ውሎ ዳሰሳችን በሳምንቱ የሀዋሣ፣ ሆሣዕናና ሀላባ ከተሞች ገበያ ውሎን እናስቃኛችሁአለን፡፡ በሳምንቱ ከነበረው የገበያ ውሎ ነጭ ጤፍ በሐዋሣ ከተማ ኩነታሉን 1 ሺህ 37ዐ ብር በችርቻሮ የተሸጠ ሲሆን የ7ዐ ብር ቅናሽ በማሳየት በሆሣዕና ከተማ 1ሺህ 3ዐዐ ብር በሀላባ ከተማ 2ዐዐ ብር ቅናሽ በማሳየት ኩንታሉ በችርቻሮ 1ሺህ 17ዐ ብር ሲሸጥ ሰንብቷል፡፡ከብርዕ ሰብል ወደ አገዳ ሰብል ስናመራ በቆሎ በሀላባ ከተማ ኩንታሉን በችርቻሮ 43ዐ ብር ተሽጧል፡፡ በሆሣዕና የ1ዐዐ ብር ጭማሪ በማሳየት 53ዐ ብር እንደዚሁም በሐዋሣ ከተማ 54ዐ ኩንታል በችርቻሮ ንግድ ተሽጧል፡፡ ወደ ጥራጥሬ እህል የገበያ ውሎ ስንሸጋገር ደግሞ አንድ ኩንታል አተር በሐዋሣ ከተማ በችርቻሮ 1ሺህ 62ዐ ብር ሲያወጣ በሆሣዕና ከተማ 12ዐ ብር ቅናሽ በማየት የ1ሺህ 5ዐዐ ዋጋ አውጥቷል፡፡ በሀላባ ገበያ በመሸጥ ከሆሣዕና ገበያ 14ዐ ጭማሪ ተስተውሏል፡፡የአትክልትና የስራስር ተክሎች ሳምንታዊ የገበያ ውሎን ስንመለከት አንድ ኪሎ ቲማቲም በሆሣዕና ከተማ 12 ብር ሲሸጥ የሰነበተ ሲሆን በሀላባ ከተማ የ3.5ዐ ሳንቲም በሀዋሣ ከተማ ደግሞ የ4 ብር ቅናሽ በማሳየት ተሽጧል፡፡ ቀይ ሽንኩር 1 ኪሎ ግራም በሐዋሳ ከተማ በችርቻሮ ተሽጧል፡፡ በሆሣዕናና በሀላባ ከተሞች ደግሞ የ9 ብር ዋጋ አውጥቷል፡፡ ነጭ ሽንኩርት በሆሣዕና ከተማ 1 ኪሎ 5ዐ ብር በሀላባ 46 ብር እንደዚሁም የሀዋሣ ከተማ የ14 ብር ቅናሽ በማሳት በ3

ሃዋሳ ከነማ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዛሬ የ2ኛ ዙር የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን በአየር ሀይል ሜዳ ይጀምራል

Image
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዛሬ መጋቢት 12/2004 ዓ.ም 9 ሰዓት ቢሾፍቱ ላይ አየር ሀይል እና የሀዋሳ ከነማ ይጫወታሉ፡፡ ባለፈው ቅዳሜ በፕሪምየር ሊግ ቀሪ ተስተካከይ ጨዋታ በቅዱስ ጊዮርጊስ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት የተሸነፈው አየር ሀይል የሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን በሜዳው ሀዋሳ ከነማን በማስተናገድ ይጀምራል፡፡ አሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተናን በማሰናበት አሰልጣኝ ንጉሴ ደስታን የቀጠረው አየር ሀይል በፕሪምየር ሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በ9 ነጥብ እና 10 የግብ እዳ 14ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመከላከያ በ2ኛው ዙር በመጀመሪያ ሳምንት ዛሬ መጋቢት 12/2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታድየም የሚያካሂዱት ጨዋታ ለሰኔ 12/2004 ዓ.ም እንደተላለፈ የኢትዮጰያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡ ፕሪምየር ሊጉን ቅዱስ ጊዮርጊስ በ30 ነጥብ ይመራል መብራት ሀይል በ28 ነጥብ ይከተላል፡፡ ደደቢት በ26 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡የኮከብ ጎል አግቢነቱን ጌታነህ ከበደ ከደደቢት በ13 ጎል ይመራል፡፡መድሀኔ ታደሰ ከኢትዮጵያ ቡና በ11 ጎል ይከተላል፡፡

የዓለም ቡና ዋጋ ማሽቆልቆል በአገር ውስጥ ግብይት ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ ነው

Image
በዓለም የቡና ዋጋ ማሽቆልቆል የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለፈው ሳምንት እስከ 12 በመቶ ድረስ አውርዶት የነበረውን ዝቅተኛውን የመገበያያ ዋጋ ገደብ እንደገና ወደ አምስት በመቶ እንዲወርድ አደረገ፡፡ ምርት ገበያው ባሳለፍነው ሳምንት ዝቅተኛውን የግብይት ወለል ወደ 12 በመቶ እንዲወርድ ያደረገው፣ በዓለም አቀፍ ገበያ የቡና ዋጋ እየወረደ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ የአገር ውስጥ ግብይትም በተመሳሳይ ሁኔታ መቀነስ ይጠበቅበት ስለነበረ ነው ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር እሌኒ ገብረ መድኅን ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በአሁኑ ጊዜ እየታየ ያለው ዓለም አቀፍ የቡና የዋጋ ማሽቆልቆል በአገር ውስጥ ያለውን የግብይት ዋጋ ከዓለም አቀፉ ገበያ በላይ እንዲሆን አስገድዶት ነበር፡፡ ይህም በመደረጉ በሁለት ቀናት ውስጥ የቡና ዋጋ እንዲወርድና የመጫረቻ ዋጋውም በኒውዮርክ ገበያ ካለው ዋጋ ጋር ተቀራራቢ እየሆነ በመምጣቱ፣ ለሁለት ቀናት የተሠራበት የመገበያያ ገደብ ተመልሶ ወደ አምስት በመቶ ዝቅ እንዲል መደረጉን ዶ/ር እሌኒ አስረድተዋል፡፡ በምሳሌ ያቀረቡትም ባለፈው ሳምንት አንድ ሺሕ ብር ዋጋ የነበረው ቡና ከለውጡ በኋላ ዋጋው ወደ 900 ብር እንዲወርድ ሆኗል በማለት ነው፡፡ ከዚህ በኋላም ግብይቱ 900 ብር ዋጋን ይዞ ከአምስት በመቶ ወደላይ ወይም ወደታች ሳይወርድ የቡና ጨረታው የሚካሄድ ይሆናል፡፡ ይህም አሁን እየወረደ ካለው ዓለም አቀፍ የቡና ዋጋ ጋር እንዲጣጣም ያደርገዋል ተብሏል፡፡ የአገር ውስጥ ግብይትን ከኒውዮርክ ገበያ ዋጋ ጋር ለማጣጣም ሲባል ባለፈው ሳምንት የተወሰደው ዕርምጃ፣ የአገር ውስጥ ዋጋን እንዲወርድ በማድረጉ እንደገና የዋጋ ገደቡን ወደ አምስት በመቶ እንዲወርድና ግብይቱ በዚሁ መንገድ እንዲቀጥል የተደረገ መሆኑንም ለማወ

የደቡብ ክልል የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመገልገል የተጠረጠሩ ኃላፊዎች ጉዳያቸው በህግ እየታየ መሆኑን አስታወቀ

Image
በደቡብ ክልል ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመገልገል በመንግስትና በህዝብ መሬትና ገንዘብ ላይ ወንጀል ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ ኃላፊዎች ጉዳያቸው በህግ እየታየ መሆኑን የክልሉ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ እንዳለው በተጠርጣሪዎቹ እና በግብረአበሮቻቸው የተመዘበረ የመንግስት መሬትና ገንዘብን የማስመለስ ስራም ተጠናክሮ ቀጥሏል። የአዲሱ መሸሻን   ሪፖርት   ከቀጣዩ   ቪዲዮ   ይመልከቱ፡፡ http://www.ertagov.com/amerta/erta-news-archive/49-erta-tv-hot-news-addis-ababa-ethiopia/1859-2012-03-16-16-51-48.html

Previously Missed Hearing on Awassa Hotel Adjourned for Investigation

Image
Justices at the Federal Supreme Court adjourned the hearing of an appeal in the case between the Privatisation & Public Enterprises Supervising Agency (PPESA) and United Africa Group (UAG) by a little over a month, for further investigation. The parties have been locked in a courtroom battle since June 2010, after lawyers from the Agency instituted a suit at the Federal High Court, involving a claim of close to 700,000 Br in punitive damages. The Group, which acquired a state property in Hawassa Town, has failed to honour its contractual obligations. lawyers claim, UAG, established in 1992 by Haddis Tilahun, an Ethiopian residing in Namibia for 18 years, and his Namibian wife, Marta Namumdjebo, pledged to renovate Awassa Lakeside Hotels (Number One), formerly under the Wabe Shebelle Hotels brand, after it acquired it from the Agency in May 2005 for 6.95 million Br. The company acquired the only property it has in Ethiopia now, agreeing to spend a total of 18 million Br

lemboo e'ama ቆንጆ ኣይቼ ከሲዳማ

New http://www.habeshazefen.com/music/musiclist/musicnew.html?tags=http://www.habeshazefen.com/music/listenmusic/1546/konjo-aychy-ke-sidama--debub.html

የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት ኣቶ ሽፈራው ሽጉጤን በኣምባሳደር ማርቆስ ተክሌ ለመተካት የሲዳማን ህዝብ የማሳመን ስራ በምስጥር በመሰራት ላይ መሆኑ ተሰማ::

በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ክልል የተከሰተው የፖለቲካ ኣለመረጋጋትና ኣለመተማመን ያሰጋው የኢህኣዴግ ኣገዛዝ ኣቶ ሽፈራው ሽጉጤን ከሃላፊነታቸው ለማንሳት የሲዳማን ህዝን የማሳመን ስራ ጀምሯል:: ታማኝ ምንጭች እንዳሉት ኣቶ ሽፈራውን እንዲተኩ በጃፓን የኢትዮጵያ በኣምባሳደር ማርቆስ ተክሌ ታጭተዋል:: ዝርዝር ዜናውን የምቀጥለው ሊንክ ተጭነው ይመልከቱ: ምንጭ :  http://www.ethiolion.com/   http://www.ethiolion.com/Pdf/031112_Shiferaw_Shigute.pdf

በሐዋሳ ከተማ ህገወጥ ነጋዴዎችና ፖሊሶች ሲታኮሱ አደሩ

የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል ዋና ከተማ በሆነችው ሐዋሳ፣ ባለፈው ረቡዕ ምሸት ፖሊሶችና የኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ሲታኮሱ አደሩ፡፡ በተደረገው የተኩስ ልውውጥ የደረሰውን የጉዳት መጠን ለማወቅ ባይቻልም አንድ ህፃን መቁሰሉን የክልሉ ፖሊስ አስታውቋል፡፡በከተማው ሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኘውና በተለምዶ ገበያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ፣ ባለፈው ረቡዕ ከምሽቱ 4፡30 ላይ የተጀመረው የተኩስ ልውውጥ እስከ ሌሊቱ ስምንት ሰዓት ድረስ ቀጥሎ መቆየቱንና በዚህ ምክንያትም የተመቱና የቆሰሉ ሰዎች በአዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው እንደቆዩ ምንጮች ለአዲስ አድማስ አስታውቀዋል፡፡ የተኩስ ልውውጡ መንስኤ ከኮንትሮባንድ ንግድ ጋር የተገናኘ መሆኑን የገለፁልን የክልሉ የወንጀል መከላከል ዋና የሥራ ሂደት ባለቤት ኮማንደር በላይነህ በላይ፤ በህገወጥ መንገድ የገቡና የተከማቹ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች እንዳሉ ለፖሊስ ጥቆማ ደርሶት ወደ ስፍራው እንደሄዱ ተናግረዋል፡፡ ቦታው ሲደርሱ ኮንትሮባንድ ነጋዴዎቹ ያደራጇቸውና ኮንትሮባንድ ዕቀዎቹን በመጫን፣ በማውረድና በመበለት ሥራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች በጉምሩክ ሠራተኞችና በፀጥታ ኃይሎች ላይ ጉዳት ለማድረስ መሞከራቸውን ኮማንደር በላይነህ ገልፀዋል፡፡ በህገወጥ ነጋዴዎቹ የተደራጁት ወጣቶች፣ መሣሪያ ታጥቀው ነበር ያሉት ኮማንደሩ፤ በፀጥታ ኃይሎቹና በጉምሩከ ሠራተኞቹ ላይ ድንጋይ በመወርወር ጉዳት ለማድረስ ከመሞከራቸውም በላይ ኦፕሬሽኑን ሠላማዊ በሆነ መንገድ ለማከናወን በሄደው የፌደራል፣ የክልሉና የከተማው የፀጥታ ኃይሎችና በጉምሩክ ሠራተኞች ላይ ተኩስ መክፈታቸውን ጠቁመው፤ በተኩስ ልውውጡ ከየትኛው ወገን እንደተተኮሰ ባልታወቀበት ሁኔታ አንድ ህፃን መቁሰሉን ገልፀዋል፡፡ ከችግሩ ጋር በተያያዘ 40 የሚደርሱ ሰዎች በቁ

Hoya Boro Boromissi by Tokichaw (Yohannes Bekele)

Image
Losse lophate kaye kamballi... Kaya kamballi kayatamaho Sidde laballi!

Hawassa in 1953 EC and 2003EC

Image
ሃዋሳ 1953 ኣ/ም ሃዋሳ 2003ኣ/ም

South Ethiopia Regional State News

http://www.smm.gov.et/   

Oromia, SNNP sign accord for peace building

Hawassa, (WIC) –  Four government institutions of the SNNP and Oromia regions today signed an agreement to coordinate activities of peace building efforts in the two regions. The agreement was signed between Nationalities Council, Security and Administration Bureau and Mass Media Agency of the SNNP region and Security and Administration Bureau of Oromia region. The agreement brings together the four institutions to utilize media outlets, radio programs in particular, to promote peace building efforts in the two regions. The programs are supported by non governmental organizations including the German Society for International Cooperation (GIZ) and the Association of Civil Societies Information Center. Speaking during the signing ceremony, Lema Guzume, speaker of Nationalities Council of SNNPR, said the radio program will be one of the many peace building activities underway in the two regions. The programs will raise the awareness of the public on the concept of peace, said

Hundimo Dedere the Sidama farmer is a model for modern bamboo cultivation and management training

Image
In Africa’s Vanishing Forests, the Benefits of Bamboo By  TINA ROSENBERG Asosa is not in China, not even in Asia.    It is a district in the west of Ethiopia, on the Sudanese border.   To many people, bamboo means China.   But it’s not just panda food — mountain gorillas in Rwanda also live on bamboo.   About 4 percent of Africa’s forest cover is bamboo . In the district of Asosa, the land is thick with bamboo.   People plant it and manage the forests. They rely on its soil-grabbing roots to stabilize steep slopes and riverbanks, cutting erosion. They harvest it to burn for fuel, to make into charcoal sticks to sell to city dwellers and to build furniture. Soon it may be much more.  Bamboo may provide a solution to a very serious problem:  deforestation.  In sub-Saharan Africa, 70 percent of the people cook their meals over wood fires.  The very poorest cut down trees for cooking fuel; those slightly less poor buy charcoal  made from wood in those same forests.

በሀዋሣ ዩኒቨርስቲ ከሁሉም የትምህርት ክፍል ለተውጣጡ ተማሪዎች በስነ ተዋልዶ ጤናና ኤች አይቪ ኤድስ መከላከል ዙሪያ ትምህርት ተሰጠ፡፡

Image
New በሀዋሣ ዩኒቨርስቲ ከሁሉም የትምህርት ክፍል ለተውጣጡ ተማሪዎች በስነ ተዋልዶ ጤናና ኤች አይቪ ኤድስ መከላከል ዙሪያ ትምህርት ተሰጠ ፡፡ስልጠናው ጤናማ፣ ብቁና አምራች ዜጋ ለመፍጠር የሚደረገው ጥረት የሚያግዝ መሆኑም ተገልጿል፡፡የሀዋሣ ዩኒቨርስቲ ኤች አይቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ዳይሬክቶሬት ረዳት ዳሬክተር አቶ አለማየሁ አበበ እንደገለፁት የስነ ተዋልዶ ጤና እና የኤች አይቪ ኤድስ ትምህርት ማግኘታቸው ከነዚህ ጋር ተያይዞ የሚጋረጡ ችግሮችን አስቀድሞ ለመከላከል ያስችላቸዋል፡፡ ዩኒቨርስቲው ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራባቸው ዘርፎች አንድ ኤች አይቪ ኤድስና የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች የተማሪዎች ችግር እንዳይሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል፡፡ከሁሉም የትምህርት ዘርፍ የተውጣጡ ተማሪዎች በመገኘታቸውም አላስፈላጊ እርግዝና እና ሌሎች በሽታዎችን ለመከላከል ያገኙትን ትምህርት ለሌሎች ተማሪዎች ግንዛቤ ለመፍጠር እንደሚያሰችልም ጠቁመዋል፡፡  ይህም ውይይት የመማር ማስተማሩን ሂደት እንዳያስተጓጉል እና ጤናማ፣ ብቁ አምራች ዜጋን ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የደቡቡ ክልል ሀገርን እንወቅ የባህል ልማትና ቱሪዝም ፎረም ዋና መስራችና ስራ አስኪያጅ ወጣት አሸናፊ ግዛው እዲህ አይነት ውይይቶች ተማሪዎች በጋራ ማድረጋቸውንና ግልጽ ሆነው የመናገር ባህል እንዲያዳብሩ ይረዳቸዋል ሲል ተናግሯል፡፡በቀጣይም እንደዚህ አይነት ፎረሞችን በክልሉ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች በማዘጋጀት እራስን ባለመጠበቅ የሚመጡ በሽታዎች በዩኒቨርስቲዎች ለመቀነስ እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡ በሌላ በኩልም ተማሪዎቹ የካምፖስ የፍቅር ሕይወት ጣጣ ወይስ አላማ በሚል ከነባራዊ ሁኔታ መነሳት ተማሪዎቹ በግልጽ ተወያይተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተስተካከይ ጨዋታ ሀዋሳ በደደቢት 1 ለ 0 ተሸንፏል

Image
New እሮብ, 14 መጋቢት 2012 13:26 በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተስተካከይ ጨዋታ ደደቢት በአዲስ አበባ ስታድየም ሀዋሳ ከነማን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ፡፡ ደደቢት ከመሪዎቹ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት አጥብቧል፡፡ የሳምሶን ከተማን ሪፖርት ከቀጣዩ ቪዲዮ ይመልከቱ፡፡ Adobe Flash Player not

Intermarriage between Conflicting Groups: The Case of the Arsi Oromo and the Sidama

2.16 Intermarriage between Conflicting Groups: The Case of the Arsi Oromo and the Sidama (Girma Negash) The basic objectives of this study can be summarized as follows:       1. To bring to light and properly document the age-long intermarriage between the Arsi and  the Sidama about whom little seem to be known thus far.       2. To investigate the puzzling paradox how two peoples who perceive one another as enemy, and often at war with each other, happen to intermarry.       3. To identify specific reasons that induced Arsi-Sidama neighbours to look for a partner  from a hostile group.       4. To analyse the attitude of members of the two respective communities towards such  cross-border marriages.       5. To examine the progress of the intermarriage issue in a time perspective.       6. To investigate the possible impact of this intermarriage on the conflict between the Arsi  and the Sidama. In pursuance of the outlined objectives of the study, a qualitativ

Gimbii Yemo!

Image
New

BET Architects snatch Hawassa University expansion design

Image
New BET Architects PLC has won a bid to design a major component of an expansion project Hawassa University will soon undertake. Hawassa University wishes to build a new university grounds including a facility it named Yirgalem Campus, for which it solicited design proposals. The university was aided by the Association of Ethiopian Architects [AEA] to select from seven entries for the three projects; civil engineering laboratory, administration building, and dormitory. The competition resulted in a big win for BET which, partnering with an international firm, has also sealed the deal to design Ethiopian Airlines’ headquarters in February.  BET took the largest of the three projects to draw a facility that houses buildings including students’ dormitory. Yohannes Abay came in second, and Sileshi Consult took third place in the competition. “BET Architects won the competition having fulfilled the client’s requirement. BET had proposed a campus development plan, and the dormi

አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአውስትራሊያ ጠቅላይ ገዢ አቀረቡ

Image
New አዲሰ አበባ, የካቲት 30 ቀን 2004 (አዲስ አበባ) - አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአውስትራሊያ ጠቅላይ ገዢ ማቅረባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡ ሚኒስቴሩ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቀው አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ ለአውስትራሊያ መንግስት ጠቅላይ ገዢ ሚስ ኩዌንቲን ብሪክ የሹመት ደብዳቤያቸውን አቅርበዋል፡፡ አምባሳደሩ የሹመት ደብዳቤያቸውን ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት የሁለቱን አገራት ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እንዲሚሰሩ በመግለጽ አውስትራሊያ ኢትዮጵያ ለተያያዘችው የልማት እንቀስቃሴ ድጋፍ እንድትሰጥ ጠይቀዋል፡፡ በወቅቱ አውስትራሊያ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር አመርቂ ውይይት መካሔዱንም አስረድተዋል፡፡ ጠቅላይ ገዢዋ ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያን መጎብኝታቸውንና በወቅቱ በአገሪቱ መንግስት ለተደረገላቸው አቀባበልና መስተንግዶ አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማእከል በመሆኗ የአውስትራሊያ አፍሪካ ዲፕሎማሲ ኢትዮጵያን ማእከል አድርጎ እንደሚንቀሳቀስም ጠቁመዋል፡፡