በቀርከሃ ተክል ላይ ያተኮረ አለማቀፍ ጉባኤ በቀጣዩ ሳምንት በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

በግብርና ሚኒስቴር የዘላቂ መሬት አያያዝ  ፕሮግራም አማካሪ አቶ መላኩ ታደሰ  እንዳሉት፥ ኢትዮጵያ ለቀርከሀ ምርት ያላት ምቹነት ጉባኤውን እንድታስተናግድ አስመርጧታል።

በጉባኤው የግሉ ዘርፍ ለቀርከሃ ልማት በሚኖረው ድርሻ እንዲሁም ቀርከሃ ለተፋሰስ ልማት በሚኖረው ሚና  ዙሪያ ጥናቶች ቀርበው ውይይት ይደረጋል።
ቀርከሀ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ለኢኮኖሚ እድገትና የህብረተሰቡን የኑሮ ደረጃ  ለመለወጥ የሚኖረው አስተዋጽኦም የጎላ መሆኑን ነው አቶ መላኩ የተናገሩት።
ኢትዮጵያ 1 ሚሊዮን ሄክታር ላይ ያረፈ የቀርከሃ ምርት ያላት ሲሆን፥ ከአፍሪካ በአጠቃላይ ካለው ምርት 67 በመቶውን ትሸፍናለች፡፡
ምንጭ፦ ኤፍ.ቢ.ሲ.

Comments

Popular posts from this blog

የሲዳማ ክልል ባለስልጣናትን ጨምሮ የተገለገሉት የሰሞኑ የቻርተር አውሮፕላን በረራዎች!

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

Reclaiming Truth: A Rebuttal to the Misrepresentation of the Sidama People’s Struggle and Cultural Legacy