በኣለማችን ላይ “ሲዳማ” የምትለውን ቃል በኢንተርኔት ላይ ሰርች የሚያደርጉ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የጎግል መረጃ ኣመለከተ።

ጎግል በኣለም ደረጃ “ሲዳማ” በምል ቃል ስለ ሲዳማ ጎግል የምያደርጉ ሰዎች ቁጥር ካለፉት ኣስር ኣመታት ጀምሮ እያደገ መምጣቱን የገለጸ ሲሆን፤ በተለይ እንደ ፈረንጆቹ ዘመን ኣቆጣጠር በ2013 ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኢንተርኔት ተጠቃሚ ሲዳማን መፈለጉ ታውቋል።

እንደጎግል መረጃ በተለይ እኣኣ ከ2007 በፊት ሲዳማ ብዙም ጎግል የተደረገ ቃል ባይሆንም፤ በ2008 ኣጋማሽ ላይ በርካታ ሰዎች “ሲዳማ”ን ጎግል ማድረጋቸው ተመልክቷል። ቀጥሎም በ2009 መጀመረያ ላይ የሲዳማ ጎልጋዮች ቁጥር የወረደ ሲሆን በተመሳሳይ ኣመት መጨረሻ ላይ እንደገና ኣድጓል።

2010 ጀምሮ የጎልጋዮች ቁጥር ኣንዴ ስያድግ ሌላ ግዜ ሲወርድ ቆይቶ በበላፈው ኣመት መጀመሪያ ላይ በታሪኩ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ መጨመሩ ታውቋል። ነገር ግን ከ2013 ኣጋማሽ ጀምሮ ይቁጥር በመውረድ ላይ ይገኛል።

ጎግል እንዳመለከተው “ሲዳማ” የምትለውን ቃል የምጎለጉሉ ሰዎች ትራፊክ በኣብዛኛው የምፈጠረው ከሰሜን ኣሜሪካ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ እና ሰሜን ኣውሮፓ ኣገራት እንድሁ የትራፊክ ምንጮች ናቸው።


የሲዳማ ጎልጋዮች ቁጥር መጨመር እና መውረድ ከሲዳማ ዞን የፖለቲካ ሁኔታ ጋር የተያያዘ መሆኑን የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ትንተና ያመለከተ ሲሆን፤ ለዚህም ማሳያ በሲዳማ ዞን ውስጥ የፖለቲካ ትኩሳት የነበረባቸው ኣመታት ማለትም በ2006 እና 2013 የተፈጠረውን ትራፊክ ማየት ይቻላል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር