የሀዋሳ ከተማ የባሀል ማዕከል ግንባታ የመጀመሪያው ምዕራፍ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል

ሀዋሳ ሚያዚያ 2/2005 በሀዋሳ ከተማ 70 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ የሚካሄደው የባህል ማዕከል ግንባታ የመጀመሪያው ምዕራፍ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ የከተማ ማዘጋጃ ቤት ገለጸ፡፡ በማዘጋጃ ቤቱ የመሰረተ ልማት ማስፋፊያ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ መብራቴ መለሰ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በሀዋሳ መስቀል አደባባይ በ2003 ሀምሌ የተጀመረው የማዕከሉ ግንባታ ሁለገብ አዳራሽ፣ አንፊ ቲያትር ቤትና ሙዚየም አካቶ የሚይዝ ነው፡፡ በተለይ ቲያትር ቤቱን ይዞ 1500 መቀመጫ የሚኖረውና ለሁለገብ የስብሰባ አገልገሎት የሚውለው አዳራሽ የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ ሲሆን በእስካሁን እንቅስቃሴ ከአጠቃላይ ስራው 80 በመቶው መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ የቀሩት ጥቃቅን ስራዎችና የውሰጥ ድርጅት ማሟላት እስከ መጪው ሰኔ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ አመልከተው ሁለተኛው ምዕራፍ የሆነውና በ30 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄደው የሙዚየሙን ግንባታ ለመጀመር ዝግጅት መጠናቀቁንና ስራው እሰከ መጪው አመት መግቢያ ድረስ እንደሚጠናቀቅ አስረድተዋል፡፡ የባህል ማዕከሉ መገንባት ሀዋሳ የቱሪዝም ከተማ እንደመሆኗ በኢንተርናሽናልና በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄዱ ስብሰባዎችን በብቃት በማስተናገድ የቱሪዝም ኮንፍራስ ከተማናቷን ከማሳደግ በሻገር የክልሉ ባህላዊ ቅርሶችና እሴቶችን አሰባስቦ ፣ ጠብቆና ተንከባክቦ ለማቆየት ከፍተኛ አስተዋጾኦ እንደሚኖረው አስተባባሪው ገልጸዋል፡፡ ማዕከሉ የቢዝነስና ማንጅመንት ፕላን ይኖሩታል ብለዋል፡፡ 
Source: http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=6846&K=1

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር