ዛሬ ሲዳማ ቡና ከ መብራት ኃይል በኣዲስ ኣበባ፤ ሃዋሳ ከነማ ከሙገር ስሚንቶ በሃዋሳ ይጫዋታሉ
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) 21ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በተለያዩ ጨዋታዎች ይቀጥላል። በዚህም መሰረት በዛሬው ዕለት በ9 ሰዓት መብራት ሃይል ከሲዳማ ቡና በአበበ በቂላ ስታዲየም ሲጋጠሙ ፥ ደደቢት ከዳሸን ቢራ ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሀረር ቢራ በተመሳሳይ ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ።
በክልል ጨዋታዎችም ሃዋሳ ላይ ሀዋሳ ከነማ ከሙገር ስሚንቶ እንዲሁም ወላይታ ዲቻ ከአርባምንጭ ከነማ ይገናኛሉ።
አምስት ጨዋታዎች ብቻ በሚቀሩት ሻምፕዮናው ፥ የሊጉን ዋነጫ ለማንሳት ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ነጥብ ብቻ ያስፈልገዋል።
Comments
Post a Comment