በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ በተያዘው የምርት ዘመን ከ171 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ::




በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ በተያዘው የምርት ዘመን ከ171 ሺህ  ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ::
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ ጋቤራ ለወረዳው ምክር ቤት 3ኛ ዙር 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ባቀረቡት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ምርቱ የተሰበሰበው በ6 ሺህ 5 መቶ 9ዐ ሄክታር መሬት ላይ ከተመረቱ በቆሎ፣ ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ቦሎቄና ከሌሎች ሰብሎች መሆኑን ገልፀዋል::በምርት ዘመኑ 625 ሺህ የቡና ችግኞች ለበልግ የተከላ ወቅት መዘጋጀታቸውን የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው በ156 ሄክታር መሬት ላይ የነበሩ ያረጁ የቡና ተክሎች ተጐንድለዋል::2ዐ ኩንታል የቡና ዘር መዘጋጀቱን ተናግረዋል::
በወረዳው የተሻሻሉ ምርጥ የከብት ዝሪያዎችን ለማርባት 82 ከብቶች በሰው ሠራሽ ዘዴ፣ 447 ደግሞ በኮርማ መዳቀላቸውን አውስተው የእንስሳት በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል በተደረገው ጥረት ለ6 መቶ ከብቶች ክትባት መሰጠቱን ገለፀዋል::ሪፖርተራችን ካሳ ጀንቦላ ከበንሳ ቅርንጫፍ እንደዘገበው::

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር