Posts

የፀረ ኤች አይ ቪ መድሃኒት በሀገር ውስጥ ሊመረት ነው

Image
የፀረ ኤች አይ ቪ መድሃኒት በሀገር ውስጥ ሊመረት ነው ፡፡ በሀገር ደረጃ የኤች.አይ.ቪ (ኤድስ) ስርጭት እየቀነሰ ቢመጣም ተጠናክሮ መሰራት እንዳለበት ተጠ ይቋል ፡፡ በኤች.አይ.ቪ(ኤድስ) ላይ የሚሰሩ የተለያዩ አካላት በጋራ የሰጡት መግለጫ ከገጠሩ ይልቅ በከተማ የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመቆጣጠር በሰፊው መሰራት አለበት ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ጤናና ስነ-ምግብ ኢኒስቲትዩትን በመወከል ዶ/ር ይበልጣል አሰፋ በተለይም በፀረ የኤች.አይ.ቪ መድሃኒት አጠቃቀም ላይ በሰፊው መስራት እንደሚፈልግ ነው የገለፁት፡፡ ዶ/ር ይበልጣል እንደሚሉት የፀረ የኤች.አይ.ቪ መድሃኒት አጠቃቀም እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም በተለይ በመረጃ አሰጣጥ ላይ ትኩረት ሊደረግ ይገባል ብለዋል፡፡ የጸረ ኤች.አይ.ቪ (ኤድስ) መድሀኒትን በ2007  መጨሻ ላይ በሀገር ውስጥ ለማምረት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም የኢትዮጵያ ጤናና ስነ-ምግብ ኢንስቲትዩት አስታውቋል፡፡ ቅደመ ዝግጅቱ ሲጠናቀቅም 5 የጸረ ኤች.አይ.ቪ (ኤድስ) መድሀኒት አምራች ፋብሪካዎች ወደ ስራ ሊገቡ እንደሚችሉም ተጠቁሟል፡፡ የፌደራል ኤች.አይ.ቪ (ኤድስ) መከላከያና መቆጣጠሪያ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ም/ዳይሬክተር አቶ መስቀሌ ሌራ እንደሚሉት ደግሞ የኤች.አይ.ቪ (ኤድስ) ስርጭቱ ለስራ በሚንቀሳቀሰው ወጣቱ ላይ ጎልቶ ይታያል፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ተወካይ ዶክተር ፍሬሕይወት መብራቱ በበኩላቸው እስከአሁን ድረስ ኤች.አይ.ቪ (ኤድስን) በተመለከተ የተሰራው ሥራ ውጤት አያሳ በመምጣቱ ጥረቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ በተለይም ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ አዲስ እቅድ ተዘጋጅቶ ቫይረሱ ከእናት ወደልጅ እንዳይተላለፍ እንደሚሰራም ነው የገለጹት፡፡ የኤች.አይ.ቪ (ኤድስ) ሥርጭትን በተመለከተ ከወንዶች ይ

የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግር ዛሬም አልተፈታም

Image
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 17 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት መቆራረጥ በመዲናችን አዲስ አበባና በተለያዩ የክልል ከተሞች እየተባባሰ የመጣ ችግር ሆኗል ። ሃገሪቱ እያመነጨች ያለው የኤሌክትሪክ ሃይል በቂ የሚባል ቢሆንም የአገልግሎት ጥራት መጓደል ግን በብዙዎች ዘንድ ተደጋጋሚ ቅሬታን እያስነሳ ነው ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን ችግሩ መኖሩን አምኖ ይቀበላል ፤ የኬርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ምህረት ደበበ እንደሚሉት ፥ የኤሌክትሪክ መቆራረጡ በማህበረሰቡና በሃገሪቱ ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት ከፍተኛ ነው። ከዚህ ቀደም ለጣቢያችን ቅሬታቸውን ያቀረቡ አካላት በየአካባቢው የሚተከሉ የሃይል ማሰራጫ ትራንስፈርመሮች ጥራት የጎደላቸው መሆን የኮርፖሬሽኑ ሰራተኞችም ፈጣን ምላሽ አለመስጠት፤ ከዚህም አለፍ ሲል እጅ መንሻ ይቀበላሉ ሲሉ ሮሮ ማሰማታቸው የሚታወስ ነው። አቶ ምህረትም  በኮርፖሬሽኑ ውስጥ መልካም ስነ ምግባር የሌላቸው ሰራተኞች መኖራቸውን በማመን ቅሬታው ተገቢ መሆኑን ይቀበላሉ። የሲቪል ሰርቪስ ሚንስቴርም ባካሄደው ጥናት  ህዝቡ ቅሬታ ከሚያሰማባቸው የፌደራል ተቋማት መካከል አንዱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን ነው። ችግሩ የኮርፖሬሽኑን አቅም እንደተፈታተነው ያመኑት ሃላፊው ጉዳዩ በመንግስት ደረጃ እየታየ መሆኑን ጠቅሰው ፥ ከዚህ ጎን ለጎንም ኮርፖሬሽኑ ማዕከላትን አደራጅቶ እየሰራ ነው ብለዋል። ይሁን እንጂ ቀድሞ የነበሩ  አሁንም ያልተፈቱና ለኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥ ምክንያት የሆኑ እክሎች እንዳሉ ናቸው። ከእነዚህ ውስጥ በስፋት እየተካሄዱ ያሉት የመንገድ ፣ የባቡርና የውሃ መስመር ዝርጋታዎች ተጠቃሽ ሲሆኑ ፥ እነዚህን መሰረተ ልማቶች ለመዘርጋት በሚደረገው ጥረት በርካታ የኤሌክትሪክ

በሀገሪቱ በኤችአይቪ\ኤድስ አዲስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር መቀነሱ ተገለፀ

Image
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 17/2005/ዋኢማ/ - በሀገር አቀፍ ደረጃ በኤችአይቪ ኤድስ አዲስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር መቀነሱን የፌዴራል ኤችአይቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የጽህፈት ቤቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ መስቀሌ ሌራ ዛሬ በጋራ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለፁት፤ በቫይረሱ አዲስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ 0 ነጥብ 9 በመቶ ቀንሷል፡፡ ለተገኘው ውጤትም መንግስት፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ህብረተሰቡ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጋቸውን ጠቁመው፤ በተለይም መንግስት ግልፅ የሆነ እስትራቴጂክ እቅድ በመቅረፅ በጠንካራ አመራር ተግባራዊ በማድረጉ ነው ብለዋል፡፡ የቫይረሱን ስርጭት ይበልጥ ለመከላልና ለመቆጣጠርም የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ በተለያዩ ዘርፎች ለማሳካት የታቀደውን እድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ከግብ ለማድረስ ወጣቱ ትውልድን ከቫይረሱ መጠበቅ እንደሚያስፈልግ አቶ መስቀሌ ተናረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ጤናና ስነ-ምግብ ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ይበልጣል አሰፋ በበኩላቸው፤ በአጠቃላይ በሀገሪቱ በቫይረሱ አዲስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየቀነሰ መምጣቱን ገልፀዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱም ስለ ኤችአይቪ ኤድስ አጠቃላይ ጥናት እንደሚያደርግ ተናግረው፤ በዚህ መሰረትም በአሁኑ ወቅት ከቫይረሱ ጋር ከሚኖሩ ሰዎች ቁጥር ውስጥ 1 ነጥብ 3 በመቶ የሚሆኑት አዋቂዎች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ የቫይረሱ ስርጭት በወንዶች 1 በመቶ ሲሆን በሴቶች ደግሞ 1 ነጥብ 9 በመቶ መሆኑን ጠቁመው፤ የቫይረሱ ስርጭት በከተማና በገጠር ያለው እንደሚለያይ ተናግረዋል፡፡ በዚህ መሰረትም በከተማ ያለው የቫይረሱ ስርጭት 4 ነጥብ 2 በመቶ ሲሆን፤ በገጠር ደግሞ 0 ነጥብ 6 መሆኑን ዶክተር ይበልጣል ገል

የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ችግር ፈቺ ከ200 በላይ የምርምር ፕሮጀክቶች እያካሄደ ነው

Image
ሃዋሳ ነሐሴ 17/2005 የሃዋሳ ዩኒቨርሰስቲ ችግር ፈቺ የሆኑ ከ200 የሚበልጡ የምርምር ፕሮጀክቶች በራሱና በውጪ ሀገራት ትብብር እያካሄደ መሆኑን ገለጠ። በዩኒቨርሰቲ የምርምር ፕሮግራም አስተባባሪ ዶክተር አለማየሁ ረጋሳ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጡት የምርምር ስራዎቻቸውን በየአመቱ በማስፋፋት በአሁኑ ውቅት 180 ፕሮጀክቶች በራሳቸው አቅምና ከ40 በላይ ደግሞ በውጪ ሀገራት ትብብር እየተካሄደ ነው። ከምርምር ፕሮጀክቶቹ መካከል ትምህርት ፣ግብርና፣ተፈጥሮ ሀብትና እፅዋት ሳይንስ፣እንስሳት ጤና፣አግሮኖሚ፣ ኑውትሪሽንና ሌሎች ማህበራዊና የኢኮኖሚ ተጠቃሜታ ያላቸው እንደሚገኙበት አስታውቀዋል። በክልሉ ወረዳዎች በተመረጡ ስድስት የቴክኖሎጂ መንደሮች የሚያካሄዳቸው ምርምር ስራዎች ከስድስት ወራት እሰከ ሶስት አመታት እንደሚቆዩ ገልጸዋል። የምርምር ስራዎቹ ችግር ፈቺና ህብረተሰብ አሳታፊ መሆናቸውን አመልክተው ህብረተሰቡን ከመጥቀም ባሻገር የመምህራንን የብቃት አቅም ያሳድጋል፣የትምህርት ጥራትን በመጠበቅ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው ገልጠዋል። ከዚህ በፊት የሚካሄዱ የምርምር ውጤቶች ሼልፍ ላይ ይቀሩ እንደነበር በማስታወስ አሁን ለህብረተሰቡ ቅርበት ባላቸው የቴክኖሎጂ መንደሮች በመሞከር በማላመድና ወደ ምርት ስራ በማሸጋገር እንዴት ጥቅም ላይ እንደሚውሉ በሰፊው እየተሰራ ነው ብለዋል። ለምርምር ስራው በዩኒቨርሰቲ በኩል 5 ሚሊዮን ብር መመደቡን አመልክተው በእያንዳንዱ የምርምር ፕሮጀክቶች ከአንድ እስከ አራት ተመራማሪዎች እንደሚሳተፉ ዶክተር አለማየሁ ተናግረዋል። ከውጪ ሀገራት ኖርዌይ፣ ካናዳ፣ አሜሪካና የሌሎች ሀገራት ዩኒቨርሰቲዎች የምርምር ስራውን በትብብር ለማካሄድ ድጋፍ እያደረጉላቸው መሆኑን ገልጠዋል። መንግሰት የጀመረው

ካላ በቀለ ዋዪ የቀድሞ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ከፍተኛ ኣመራር ከሰይፌ ነበልባል ሬድዮ ጋር በወቅታዊ የሲዳማ ፖለቲካዊ ጉዳይ ላይ ያደረጉትን ቃለ ምልልስ በተመለተከ ያላችሁን ጥያቄ እና ኣስተያየት ይላኩልን

Image
ፎቶ  https://www.facebook.com/bekele.wariyo/photos ካላ በቀለ ዋዪ የቀድሞ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ከፍተኛ ኣመራር ከሰይፌ ነበልባል ሬድዮ ጋር በወቅታዊ የሲዳማ ፖለቲካዊ ጉዳይ ላይ ያደረጉትን ቃለ ምልልስ በተመለተከ ያላችሁን ጥያቄ እና ኣስተያየት በሚከተለው ኣድራሻ ይላኩል፤ ምላሻቸውን ጠይቀን እናቀረባለን፦ nomonanoto@gmail.com  እናመሰግናለን።  ካላ በቀለ ዋዪ በቃለ ምልልሱ የተነሱ ኣንኳር ጉዳዮች በሲዳማ ህዝብ ላይ የሚደርስውን ኣስተዳደራዊ በደል  የሲዳማ ህዝብ የመልካም ኣስተዳደር  ጥያቄ የሲዳማ ህዝብ የራስ ገዝ የክልል ኣስተዳደር ጥያቄ በመንግስት ሰለመታፈን   ካላ በቀለ ዋዪ በወቅታዊው የሲዳማ የፖለቲካ ሁኔታ እና የክልል ጥያቄ በተመለከተ ከሰይፌ ነበልባል ሬድዮ ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ

“Sidama Camping”, Year 2

Image
This past weekend we went camping in Southeastern New Hampshire with a group of Ethiopian adoptive families — our second straight year. The core group of campers go way-back and have mid-teenaged girls, but they open the camping to any Ethiopian adoptive families, and Little Boy has such a blast last year with the older kids that we could not say “No” to  a second year. He calls it “Sidama camping,” because that’s what we call it, because more than a few of the kids are of Sidama origin and bear a strong physical resemblance to Little Boy. http://www.meredithgreen.com/?p=8904 source:  http://www.meredithgreen.com/?p=8904

SIDAMA PEOPLE: ETHIOPIA`S KUSHITIC EXPERT COFFEE GROWERS

Image
The Sidama people agricultural and semi-pastoral Kushitic people living in the southern part of the Ethiopia, in the Horn of Africa. The majority of the Sidama people live in the Southern part of Ethiopia with notable geographical features like lake Awassa in the North and lake Abaya in the South. Sidama region of Ethiopia is home of the Sidamo Coffee. The area is characterised by lush green countryside making it known as the Garden of Ethiopia. The Sidama along with Agew and Beja were the first settlers in the northern highlands of the present day Ethiopia before the arrival of Yemeni habeshas (Abyssineans). The Sidama people and their sub-tribes ( major Sidama group, Alaba, Tambaro, Qewena and Marakoare) are estimated to be around 8 million; constituting 4.01%  of the Ethiopian population and are the fifth largest ethnic group in Ethiopia.                                       Beautiful Sidama tribe woman from Sidama region, Ethiopia Like other comparable communities, th

በመኸር እርሻ ሥራ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደገ እየሰሩ መሆናቸውን በሲዳማ ዞን የጐርቼ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለፁ፡፡

በወረዳው በ2ዐዐ5 እና በ2ዐዐ6 ዓ/ም የመኸር እርሻ ከ3 ሺህ 57ዐ  ሄክታር በላይ መሬት በዋና ዋና ሰብሎች ዘር ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡፡ አርሶ አደር አመሎ ኪቦ አና አርሶ አደር ቀጤ ወጀቦ በወረዳው የሐርቤ ሚቀና ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ የመኸር እርሻ ሥራን ውጤታማ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ገልፀው በተለያዩ ጊዜያት ባገኙት የክህሎት ሥልጠና በመጠቀም ጥምርታቸውን በጠበቀ መልኩ በመዝራት ላይ እንዳሉ ተናግረዋል፡፡ የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ስጦታው ከንባታ በበኩላቸው በ2ዐዐ5 እና በ2ዐዐ6 ዓ/ም የመኸር እርሻ ከ3 ሺህ 57ዐ ሄክታር በላይ መሬት በዋና ዋና የሰብል ዘሮች ለመሸፈን የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝና እስከ አሁንም 3 መቶ 36 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈናቸውን ገልፀዋል፡፡ በመኸር እርሻ በዘር ከሚሸፈን ማሳ አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል ሲል የዘገበው የወረዳው የመንግሰት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው፡፡ ምንጭ፦ http://www.smm.gov.et/_Text/13NehTextN805.html

በሲዳማ ዞን ጐርቼ ወረዳ የሚገኙ የመንግስት ሠራተኞች የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር የአቶ መለስ ዜናዊ የአረንጓዴ ልማት ፖሊሲ እውን ለማድረግ ከ12 ሺህ በላይ ችግኝ ተክለዋል፡፡

Image
በችግኝ ተከላው የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰንበቱ ተካ የአረንጓዴ ልማት ቀያሽ ከሆኑት ከቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስተር የተጀመሩ ልማቶችን ለማስቀጠል ህዝቡና አመራሩ ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ህብረተሰቡም  በችግኝ ተከላውና በፓርክ ምስረታው ላይ ያሳየውን ቁርጠኝነት በእንክብካቤ ስራው ላይም አጠናክሮ ሊቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡ በችግኝ ተከላው ወቅት ያነጋገርናቸው አንዳንድ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርን የአረንጓዴ ልማት ፖሊሲ ለማሳካት የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልፀዋል፡፡ በወረዳው በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ስም በሁሉም ቀበሌያት ፓርኮች ተቋቁመዋል ከ12 ሺህ በላይ ችግኞችም ተተክለዋል ሲል የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዘግቧል፡፡ የዞኑ ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ አሸብር ልሳኑ በበኩላቸው ከፓርኩ የሚገኘው ገቢ በዚሁ አካባቢ ለሚገኙ ማህበረሰቦች የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች እንደሚሟሉበት ተናግረው  ህብረተሰቡ ፓርኩን በባለቤትነት እንዲቆጣጠርም ጭምር አሳስበዋል፡፡ በዚሁ ዙሪያ ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በተደረገ ውይይት ፓርኩ የማንም ሳይሆን የራሳችን በመሆኑ ከዚህ በኃላ የሚፈጠረውን ጥቃት ለመከላከል ወንጀለኞችን አሳልፈን ለህግ እንሠጣለን ሲሉ የሀገር ሽማግሌዎች ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ኦሞ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ አንደዘገበው፡፡ ምንጭ፦ http://www.smm.gov.et/_Text/13NehTextN705.html

የባንኮች የውጭ ምንዛሪ ግዢና አጠቃቀም ግልጽነት ይጐድለዋል

Image
የኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ከሚያገኝባቸው ምንጮች መካከል የውጭ ንግድ (Export) እና በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በባንኮች በኩል የሚልኩት ገንዘብ (Remittance) ዋናዎቹ ናቸው፡፡ መንግሥት የውጭ ንግዳችን እንዲያድግና ለገቢ ንግዳችን (Import) የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት ሰፊ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በዋናነት በቡና ላይ ተመሥርቶ የነበረው የውጭ ንግዳችን ዛሬ መሠረቱ ሰፍቶ አበባ፣ ቆዳ፣ ጨርቃ ጨርቅ፣ የቅባት እህሎች፣ የቁም ከብቶችና ሌሎችም ተጨምረዋል፡፡ በውጭ ንግድ ላይ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች መሬት በአነስተኛ ዋጋ ከማቅረብ ጀምሮ ከውጭ የሚያስገቧቸው መሠረታዊ ዕቃዎች በአብዛኛው ከቀረጥና ታክስ ነፃ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ላኪዎች ገንዘብ ከባንኮች በአነስተኛ ወለድ ያገኛሉ፡፡ ከባንኮች ለሚበደሩት ገንዘብም መንግሥት ዋስትና የሚሰጥበት አግባብ አለ፡፡ ምርታቸውንም ተወዳዳሪ እንዲሆን ያለምንም ቀረጥና ታክስ ወደ ውጭ አገር ልከው እንዲሸጡ ይፈቀድላቸዋል፡፡ ታዲያ ይህ ሁሉ ማበረታቻ ተደርጎለት የሚገኝ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀም ላይ ክፍተት ይታያል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ አገር ገንዘቦች መግዣና መሸጫ ዋጋን ይወስናል፡፡ የየቀኑ የውጭ ምንዛሪ መግዣና መሸጫም ዋጋም በሬድዮና በቴሌቪዥን ከምንስማው ባፈነገጠ መልኩ ባንኮች ከመግዣ ዋጋ በተጨማሪ በመግዣና በመሸጫ መካከል ባለው ዋጋ (Mid rate)፣ አንዳንዴም በመሸጫ ዋጋ (Selling rate) ከላኪዎች (Exporters) እንደሚገዙ ይሰማል፡፡ በተለይ የዚህ ዓይነት የውጭ ምንዛሪ ግዢ በአገሪቱ የጠረፍ ከተሞች በኩል ከሚወጡ ዕቃዎች ሽያጭ በሚገኝ የውጭ ምንዛሪ ላይ እንደሚበረታታ ውስጥ አዋቂዎች ይገልጻሉ፡፡ አፈጻጸሙም ግልጽነት የጎደለው፣ ሙስ

Year after leader dies, Ethiopia little changed

Image
ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — Residents in Ethiopia's capital awoke to the sound of a 21-gun salute Tuesday to mark the first year anniversary of the death of long-time ruler Meles Zenawi. The ritual underscores the approach Meles' successors have employed during the last year: a continued lionization of the late prime minister, whose portrait still appears in every public office across the country. Candlelit vigils and the launch of over two dozen parks were organized across the country for the late leader. In the capital a cornerstone for the Meles Zenawi Memorial Museum was laid in a televised ceremony. During the ceremony, attended by regional leaders such as the presidents of Somalia and Sudan, Meles was praised as "Africa's voice." His successor Prime Minister Prime Minister Hailemariam Desalegn praised Meles as a "champion of the poor." "Meles did a remarkable endeavor in the green economic development. He also led a successful par

ካላ በቀለ ዋዪ የቀድሞ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ከፍተኛ ኣመራር ከሰይፌ ነበልባል ሬድዮ ጋር በወቅታዊ የሲዳማ ፖለቲካዊ ጉዳይ ላይ ያደረጉትን ቃለ ምልልስ በተመለተከ ያላችሁን ጥያቄ እና ኣስተያየት ይላኩልን

Image
ፎቶ  https://www.facebook.com/bekele.wariyo/photos ካላ በቀለ ዋዪ የቀድሞ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ከፍተኛ ኣመራር ከሰይፌ ነበልባል ሬድዮ ጋር በወቅታዊ የሲዳማ ፖለቲካዊ ጉዳይ ላይ ያደረጉትን ቃለ ምልልስ በተመለተከ ያላችሁን ጥያቄ እና ኣስተያየት በሚከተለው ኣድራሻ ይላኩል፤ ምላሻቸውን ጠይቀን እናቀረባለን፦ nomonanoto@gmail.com  እናመሰግናለን።  ካላ በቀለ ዋዪ በቃለ ምልልሱ የተነሱ ኣንኳር ጉዳዮች በሲዳማ ህዝብ ላይ የሚደርስውን ኣስተዳደራዊ በደል  የሲዳማ ህዝብ የመልካም ኣስተዳደር  ጥያቄ የሲዳማ ህዝብ የራስ ገዝ የክልል ኣስተዳደር ጥያቄ በመንግስት ሰለመታፈን   ካላ በቀለ ዋዪ በወቅታዊው የሲዳማ የፖለቲካ ሁኔታ እና የክልል ጥያቄ በተመለከተ ከሰይፌ ነበልባል ሬድዮ ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ

እነ “ሻኪራ” በአሞራ ገደል

Image
የዛሬ ሳምንት ሀዋሳ ነበርኩኝ፡፡ የወትሮዋ ሳቂታዋ ሀዋሳ አልነበረችም፡፡ አኩርፋለች፡፡ ሌላ ችግር ገጥሟት ግን አይደለም፡፡ ክረምቱ ነው ያስኮረፋት፡፡ ዝናቡ፣ ቅዝቃዜውና ደመና የሸፈነው ሰማይ ተጫጭነዋት ነበር፡፡ እንደኔ እንደኔ ሀዋሳ ደርሶ አሞራ ገደልን ሳይጐበኙ መመለስ ካለመሄድ እኩል ነው፡፡ እዚህ ስፍራ ዓሳ እንደጉድ ይበላል፡፡ ያውም ቁጥር - ልክ እንደ ስጋ፡፡ የአሳ ቁርጥ ተመጋቢዎች በእንጨት ግድግዳ በተከበበው ዳስ መሳይ ቤት ውስጥ ግፊያውና መረጋገጡን ተያይዘውታል፡፡ በሀዋሳ ሀይቅ ዳር ባለው በዚህ ስፍራ ሰው ከአንድ ቦታ አሳውን ይገዛና እዛው ዳስ ቤት ውስጥ የአሳውን እሾክ እያስወጣ ቁርጡን በሳህን እየያዘ ማባያውን ለማግኘት ሁለት ጐን ለጐን የተቀመጡ ማባያ አቅራቢዎች ጋር መገናኘት ይጠበቅበታል፡፡ አንዱ “ዳጣ” የተባለው እና ከሚጥሚጣ እንዲሁም ከሌሎች ቅመሞች የተሰራ የሚያቃጥል ማባያ ሲሆን (እኔ በጣም ከማቃጠሉ የተነሳ “እንላቀስ” ብየዋለሁ) ሁለተኛው ትንንሽ ክብ የበቆሎ ቂጣዎች ናቸው፡፡ ሁለት ወጣቶች የአሳ ቁርጥ ከግፊያው ውስጥ ይዘው ወጥተው አንዱ ሌላውን፣ “ሂድና ሲዲ ይዘህ ና፣ ታዲያ ስክራች እንዳይኖረው” ሲል አስጠነቀቀው፡፡ ሲዲ ምንድነው ስል ጠየቅሁት አንዱን ወጣት፡፡ “ሲመጣ ታይዋለሽ” አለና ዳጣ ሊያስጨምር መስከረም ወደ ተባለች ዳጣ ሻጭ አመራ፡፡ እኔም ስክራች እንዳይኖረው የተባለውን ሲዲ በጉጉት መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ ለካስ ሲዲ የሚሉት የበቆሎውን ቂጣ ነው፡፡ “ስክራች” የተባለው ደግሞ ያረረ እና የተሰነጣጠቀ እንዳይሆን ለማለት የተጠቀሙበት አገላለፅ ነው፡፡ ከወጣቶቹ የእንብላ ግብዣ ቀረበልኝ፡፡ የአሳ ቁርጥ በልቼ ስለማላውቅ ብፈራም “ሲዲ”ውን በዳጣ ግን አልማርኩትም፡፡ ወጣቶቹ ቁርጡን እየበሉ ሳሉ አንዱ “ሲዲውን በርን (burn)

በሲዳማ ዞን ከ424 ሺህ ለሚበልጡ ህፃናት የተለያዩ በሽታዎች መከላከያ ክትባት ተሰጠ ተባለ

ሃዋሳ ነሐሴ 15/2005 በሲዳማ ዞን በተጠናቀቀው የበጀት አመት ከ424 ሺህ ከሚበልጡ ህፃናት የተለያዩ በሽታዎች መከላከያ ክትባት መሰጠቱን የዞኑ ጤና መምሪያ አስታወቀ ። በመምሪያዉ የጤና ልማት እቅድ የስራ ሂደት ኦፊሰር አቶ አበበ በካዬ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጡት መንግሰት ለህፃናትና እናቶች ጤና መጠበቅ በሰጠው ትኩረት በሽታን አስቀድሞ የመከላከሉ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ። በዞኑ 19 ወረዳዎችና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች እድሜያቸው ከአንድ አመት በታች ለሆናቸዉ 424 ሺህ 126 ህፃናት የፖሊዮ ፣ የቲቢ፣ የኩፍኝና የሳንባ ምች በሽታ መከላከያ ክትባት መሰጠቱን አስታዉቀዋል ። በዞኑ በመደበኛ የክትባት አገልግሎት በበጀት አመቱ 105 ሺህ 910 ህፃናት መከተባቸውንም አስረድተዋል። በተጨማሪ 15 ሺህ ለሚሆኑ ከፍተኛ ምግብ አጥረት ችግር ላለባቸው ነፍስጡር እናቶችና ህፃናት የተለያዩ አልሚ ምግቦች እንደተሰጣቸውና ከ 80 ሺህ ለሚበልጡ ህፃናት የቫይታሚን ኤ እደላ መደረጉንም አስረድተዋል። http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=11072&K=1

የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረትና የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲዎች ውህደት ፈፀሙ

አዲስ አበባ ነሐሴ 15/2005 የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረትና የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲዎች ውህደት መፈጸማቸውን ትናንት አስታወቁ። የኢትዮጵያ ማሕበረ ዴሞክራሲ-ደቡብ ኅብረት አንድነት ፓርቲ (ኢማዴ-ደህአፓ) በሚል አዲስ ስያሜ ውህደቱን ይፋ ያደረገው ይኸው ፓርቲ የፀረ-ሽብር ሕጉን እንደሚቃወም አስታውቋል። የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጥላሁን እንደሻው ውህደቱን አስመልክቶ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳሉት ሁለቱ ፓርቲዎች በአገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ በነበራቸው የጋራ አቋም ራዕያቸውን በጋራ ለማሳካት ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል። የኢትዮጵያ ማሕበረ ዴሞክራሲ-ደቡብ ኅብረት አንድነት ፓርቲ (ኢማዴ-ደህአፓ) ሕጋዊ ሰውነት እንዲያገኝ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ በማቅረብ ቦርዱ ሰኔ 3 ቀን 2005 ዓ.ም የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት መስጠቱን ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ውህደቱን በትናንትው ዕለት ይፋ ያደረገው ይኸው ፓርቲ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ በአገሪቱ ተግባራዊ የሆነውን የፀረ-ሽብር ሕግን እንደሚቃወም አስታውቋል። እንደ አቶ ጥላሁን ገለፃ የፀረ-ሽብር ሕጉ ሠላማዊ የሕዝቦች ተቃውሞን የማፈን ባህሪይ ስላለው ፓርቲያቸው እንደ ሌሎች የመድረክ አባላት ሁሉ ሕጉን ይቃወማል። ፓርቲው በማኒፌስቶው በግልጽ እንዳስቀመጠው የፀረ-ሽብር ሕጉ የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን የሚጋፋ በመሆኑ ሕጉን አጥብቆ እንደሚቃወም ገልጸዋል። በዚህም በኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤት እንዲቋቋም ፓርቲው ከመፈለግ ባሻገር ትግል እንደሚያደርግ አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ማሕበረ ዴሞክራሲ-ደቡብ ኅብረት አንድነት ፓርቲ የኃይማኖት አክራሪነትን፣ የኃይማኖታዊ መንግሥት መቋቋምን እንዲሁም ኃይማ

ሕዝብ ‹‹መልካም አስተዳደር በተግባር!›› እያለ ነው

Image
መንግሥት መልካም አስተዳደር መኖር አለበት ይላል ወይ? አዎን! ኢሕአዴግም በጉባዔው ብሏል፣ በውሳኔም አሳልፏል፡፡ በየቀኑ መግለጫ ይሰጥበታል፡፡ መልካም አስተዳደር እውን የማታደርጉ ወዮላችሁ ብሏል፡፡ የመልካም አስተዳደር አለመኖር አደጋንም ገልጿል፡፡ መንግሥትም ብሏል፣ ኢሕአዴግም ብሏል፣ ሕዝብም ሰምቷል፣ አዳምጧል፡፡  ጥያቄው የተባለው፣ የተወሰነውና ቃል የተገባው መልካም አስተዳደር የት አለ የሚል ነው፡፡ የሕዝቡ ጥያቄ ‹‹መልካም አስተዳደር በተግባር!›› ነውና፡፡ በተግባር ያልታየ ነገር ‹‹ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም አላይ›› ነውና፡፡ መንግሥት በፌዴራል ደረጃም በክልል ደረጃም ወደ ተጨባጭና አሳማኝ ተግባር ይግባ፡፡ ይናገር ሳይሆን ያሳይ፡፡  በዚህ መሥሪያ ቤት ሕዝቡ መልካም አስተዳደር አላገኘም ከተባለ መንግሥት ያንን መሥሪያ ቤት ገባ ብሎ መመርመርና መፈተሽ አለበት፡፡ በመልካም አስተዳደር መጥፋት ምክንያት ያላግባብና ከሕግ ውጭ የተሰጠ ጥቅም ካለ ውሳኔው ትክክል አልነበረም በማለት፣ የወሰኑት ሰዎችም መጠየቅ አለባቸው ብሎ የማስተካከያና የእርምት ዕርምጃ መውሰድ አለበት፡፡  በመልካም አስተዳደር ምክንያት በደል የደረሰባቸው ዜጎች ካሉ ፈትሾ ያላግባብና ከሕግ ውጭ መብታቸው ተጥሷል፣ ተጎድተዋል በማለት የደረሰባቸው በደል እንዳይቀጥል አስተካክሎ፣ አርሞና ይቅርታ ጠይቆ ትክክለኛ ዕርምጃ ሊወስድ ይገባል፡፡ ያኔ ነው ሕዝብ እውነትም መልካም አስተዳደር አለ የሚለው፡፡ እውነትም ለመልካም አስተዳደር ከልብ ቆሟል ብሎ ሕዝብ የሚያምነውና ከጎኑ የሚቆመው፡፡ ስለዚህ ተግባር! ተግባር! አሁንም ተግባር! መንግሥት ለመልካም አስተዳደር መስፈን እንቅስቃሴ ሲያደርግ ሥራው ቀላልና ፈጣን ይሆንለታል ማለት አይደለም፡፡ ሴረኛ ያደናቅፈዋል፡፡ ሙሰኛና ፀረ መልካም

ኮሚሽኑ የተሿሚዎችን፣የተመራጮችንና የመንግሥት ሠራተኞች የሀብት ምዝገባ የሚይዝበትን ስምምነት ተፈራረ

Image
አዲስ አበባ ነሐሴ 14/2005 የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የተሿሚዎችን፣የተመራጮችንና በሕግ ግዴታ የተጣለባቸውን የመንግሥት ሠራተኞች የሀብት ምዝገባ በመረጃ ቋት የሚይዝበትን ስምምነት ከአንድ ኩባንያ ጋር ዛሬ ተፈራረመ። ኮሚሽኑ ሲ ኤስ ኤም ሳይበርቴክ ሶፍት ዌር ኤንድ መልቲ ሚዲያ ከተባለው የሕንድ የግል አማካሪ ተቋም ጋር የተደረገው ስምምነት ለሀብት ምዝገባው የሚያስፈልገውን ሶፍት ዌር ለማሰራት ያስችላል። ለፍትህ ሥርዓት ማሻሻያ ሥርዓት ከተመደበው 198ሺህ 530 ዶላር ድጋፍ የሚሰራው ሶፍት ዌር በፌዴራል ደረጃ የተመዘገቡ 60ሺህ አስመዝጋቢዎችን ሀብት ምዝገባ ውጤት ለሕዝብ ክፍት እንደሚያደርግም ኮሚሽኑ አመልክቷል። የሶፍት ዌር ሥራው ሲጠናቀቅ በሀብት ምዝገባው ዓዋጅ መሠረት ውጤቱን ለሕዝብ ተደራሽ ለማድረግ ከማገዙም በላይ፤በቀጣይ ሀብታቸውን የሚያስመዝግቡ ግለሰቦች ባሉበት ሆነው የመመዝገቢያውን ቅጽ በማውጣት መመዝገብ ይችላሉ። ኮሚሽኑ ከክልሎች የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽኖች ጋር ያለውን የመረጃ ልውውጥ እንደሚያቀላጥፈው መግለጹን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘገባ አስታውቋል። http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=11046&K=1

ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ውግዘትና የመንግሥት ክርክር

በመስፍን መንግሥቱ ኢሕአዴግ ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ መንግሥት በዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች የገዛ ዜጎቹን መብቶች ያለገደብ የሚጥስና ሰብዓዊ መብት የሚጥስ እየተባለ ያልተከሰሰበት ጊዜ የለም ማለት ይቻላል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ መንግሥት በዜጎች ላይ ይፈጽመዋል በሚባለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ዓለም አቀፍ ትኩረትን በሚመለከት የመጀመሪያ ምዕራፍ አይደለም፡፡ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ከተገረሰሰ በኋላ በኢትዮጵያ የተፈጸሙ የዜጎች ጅምላ ግድያዎችን ዓለም በከፍተኛ መገረም ተከታትሎ አውግዟቸዋል፡፡ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም አገዛዛቸው በኢትዮጵያ የከፍተኛ ጭካኔና የመብት ጥሰት ዘመን ሆኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ባተረፈው ታዋቂነት ምክንያት የውግዘት ዒላማ ሆኖ አልፏል፡፡  የደርግ መውደቅ በኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የፍፃሜ ምዕራፍ ይሆናል ተብሎ ተስፋ ተደርጎ ነበር፡፡ ነገር ግን አልሆነም፡፡ ከኢሕአዴግ ወደ ሥልጣን መምጣት በኋላም ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በተለይም ሒዩማን ራይት ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናል ያኔ አዲስ የነበረውን የኢትዮጵያ መንግሥት በሰብዓዊ መብት ጥሰት በማብጠልጠል ነበር የተቀበሉት፡፡ ባለፉት ሃያ ዓመታት ይህ ሥራቸው ሆኖ ዘልቋል፡፡ ጋዜጠኞችን ከመንግሥት ጥቃት በመከላከል ላይ የተሰማሩ ዓለም አቀፍ ድርጀቶችም የኢትዮጵያን መንግሥት በየጊዜው መክሰስ ሥራቸው ሆኗል፡፡ ከእነኝህ ዓለም አቀፍ  ድርጅቶች በተጨማሪ የአሜሪካ  መንግሥት ውጭ ጉዳይ መሥርያ ቤትም በየጊዜው በሚያወጣው ዓመታዊ መግለጫው የኢትዮጵያ መንግሥትን በሰብዓዊ መብት ጥሰትና የፖለቲካ መብቶችን ማፈን ሳይከስ ያለፈበት ጊዜ የለም፡፡ አሁን አሁን የእነኚህን አካላት መግለጫዎች የታወቁ ዓለም አቀፍ መገናኛ ድርጅቶች በመቀባበል