Posts

የምርት ገበያው ደካማ አሠራር ቡና አቅራቢውን እያኮላሸው መሆኑ ተገለጸ

Image
የምርት ገበያው ደካማ አሠራር ቡና አቅራቢውን እያኮላሸው መሆኑ ተገለጸ የጽሑፍ መጠን       ኢሜይል   0 አስተያየት шаблоны RocketTheme Форум вебмастеров የኢትዮጵያ ምርት ገበያ አሠራር ችግር እየፈጠረባቸውና ለከፍተኛ ኪሳራ እየዳረጋቸው መሆኑን የቡና አቅራቢዎች በተደጋጋሚ ሲገልጹ መቆየታቸው የሚታወቅ ሲሆን በተለይ የሲዳማ ቡና አቅራቢዎች ማኅበር ለችግሩ መፍትሔ እንዲሰጠው ጥያቄ ማቅረቡ ታውቋል፡፡ ማኅበሩ በቅርቡ በሐዋሳ ከተማ ባካሄደው ስብሰባ፣ በሐዋሳ የሚገኘው የምርት ገበያው ማዕከል፣ አደረሰብን ያሉትን ችግር በዝርዝር በማስቀመጥ፣ ይህንን ችግር እንዲፈታላቸው ለመንግሥት አቤት ብለዋል፡፡  በስብሰባው ወቅት እንደተገለጸውና መንግሥት እንዲያውቅልን በማለት በጽሑፍ ያዘጋጁት መረጃ እንደሚያሳየው፣ ችግሩ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጀምሮ የተዛባ የቡና ጥራት ደረጃ አሰጣጥን የሚያጠቃልል ነው፡፡ የቡና ደረጃ አሰጣጥ ላይ ያለው የተዘበራረቀ አሠራር ከአቅማችን በላይ ሆኗል የሚሉት የማኅበሩ አባላት፣ ደረጃውን ጠብቆ የተዘጋጀ ቡና በአንዱ የምርት ገበያው ማዕከል ባለሙያዎች የተሰጠው ደረጃ በሌሎች ማዕከሎች ግን ደረጃውን አልጠበቀም ተብሎ ይጣልባቸዋል፡፡  ባለፉት ሁለት ወራት የሐዋሳው የምርት ገበያ መጋዘን ጥበት አጋጥሞታል በመባሉ ወደ አዲስ አበባ የላኩት ቡና፣ ሐዋሳ ላይ ደረጃ አምስት ተብሎ አዲስ አበባ ላይ ግን በጥራቱ የደረጃ ሁለት ማዕረግ እንደተሰጠ የተመደበ ሲሆን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡  እንዲህ ባሉ አግባብ ያልሆኑ አሠራሮች ምክንያት የቡና ላኪዎች ጉዳት ላይ እየወደቁ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ በዚህም ችግር አንድ ቡና አቅራቢ ድርጅት በአንድ መኪና በግምት ከ80 እስከ 100 ሺሕ ብር እየከሰረ

በተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም የአካባቢያዊ የዘር ቢዝነስ ፕሮጀክት 3 (LSB) እንቅስቃሴ

Image
ዶ/ር ሁሴን መሀመድ እባላለሁ፤በመምህርነት (በአሶሼትፕሮፌሰር ማዕረግ)፤ በዕፅዋት ማዳቀልና ዝርያ በማውጣት በአሁኑ ወቅት ደግሞ ከመምህርነት በተጨማሪነት በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም አስተባባሪ በመሆን እያገለገልኩ እገኛለሁ፡፡ የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት በጣም ሰፊ ፕሮግራም ነው፡ የዘር ዘርፍ ደግሞ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ያሳድጋሉ ከምንላቸው አስፈላጊ ግብአቶች አንዱ ነው፡፡ በፕሮግራሙ ዋና አላማችን ዓለም አቀፍ ሰብል ዝርያ አባዢ ድርጅቶችን፤ ኢትዮጵያዊና ገና በመጠናከር ላይ ያሉ የግል የዘር አባዢዎችን በተጨማሪም ተደራጅተው ዘርን አባዝተው የሚያቀርቡ የአርሶ አደር ማህበራትንና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን አቀናጅቶ ለእድገታችን ማነቆ ሆኖ የቆየውን የዘር ዘርፍ ችግርን ለመፍታት ዘርን በጥራትና በብዛት በማምረትና በማቅረብ በሀገራችን ውስጥ የጀመርነውን ፈጣን እድገት አስተማማኝ ለማድረግ ነው ፡፡ የዘር ዘርፍን ለማጠናከር የISSD ፕሮግራም የአርሶ አደር የዘር ብዜትና ግብይት ማህበራትና የግል የዘር አባዢዎችን በመደገፍ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የተመሰከረለት ዘርን (Certified Seed) መጠበቅ፤ ጥራታቸውን የጠበቁ አራቢ፤ መስራችና ቅድመመስራች ዘሮችን በምርምር ማዕከላት ደረጃ በጥራት እንዲመረቱና የአቅም ማጎልበት ስራንም ለመስራት መሰረታዊ የዘር ዘርፍ ችግርን የሚያጤን ኮሚቴ (Core Group) ከተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም፤ ከክልል ግብርና ቢሮ፤ መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች (NGO)፤ ከደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅትና፤ ከደቡብ ግብርና ምርምር ማዕከል በተወጣጡ አባላት ተቋቁሞ በዘርፉ ያሉትን ችግሮች ነቅሶ በማውጣት ለእነኚህ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት እየሰራን እንገኛለን፡፡ ቀደም ብሎ የዘርፉ መሰረታዊ ች

ዩኒቨርስቲው ሶስት አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች በድህር ምረቃ ደረጃ ሊከፍት ነው

Image
ሃዋሳ ግንቦት 03/2005 የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በ2006 የትምህርት ዘመን በድህረ ምረቃ ደረጃ አዳዲስ ፕሮግራሞችን ለመክፈት እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ፡፡ ዩኒቨርሰቲው የቅበላ አቅሙን ለማሳደግም 2 ቢሊዮን ብር በሚጠጋ በጀት የማስፋፊያ ግንባታ በማካሄድ ላይ ነው፡፡ ዩኒቨርስቲው የሚከፍታቸው አዳዲስ ኘሮግራሞች በጋዜጠኝነትና ማስ ኮሚኒኬሽን፣ በሶሻል ሳይኮሎጂ እንዲሁም በጎልማሶች ትምህርትና የህብረተሰብ ልማት ዘርፎች ነው፡፡ ለሶስቱ አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች የተቀረጹትን ስርዓተ ትምህርቶችን ለማዳበር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ በተዘጋጀው መድረክ ላይ በዩኒቨርስቲው የሶሻል ሳይንስና ሂውማኒቲስ ኮሌጅ ዲን ዶክተር ንጉሴ መሸሻ እንዳስታወቁት በድህረ ምረቃ ደረጃ የሚከፈቱት እነዚህ ፕሮግራሞች በየትምህርት ዘርፉ ሀገሪቱን ወደተሻለ አቅጣጫ እንድትጓዝ የሚያስችሉ ብቁና ተወዳደሪ ምሁራን ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጾኦ አላቸው፡፡ በተለይ በጋዜጠኝናትና ማስ ኮሚኒኬሽን የስልጠና መስክ የዕድገትና የፖለቲካ ተግባቦት ፣ የማስታወቂያና የህዝብ ግነኙነትን ሲያካትት በሶሻል ሳይኮሎጂ ዘርፍ ደግሞ ወደፊት በሀገሪቱ ስለሚኖረው የማህበረሰባዊ ስነልቦና እና ሊከሰቱ የሚችሉ ችግሮች በማጥናት ብሎም ዜጎች በትክክለኛው መንገድ እንዲገዙ ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የጎልማሶች ትምህርትና የህብረተሰብ ልማት ዘርፍም በሀገሪቱ ያልተማሩ ዜጎችን ለማብቃት የጎልማሶች ትምህርት ከማህበረሰብ እደገትና ልማት ጋር አብሮ ለማስኬድ የሚስችሉ ብቁ ሙሁራን ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጸኦ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በፈጣን የእድገት እንቅስቃሴ ላይ የሚገኘው የሀዋሳ ዩኒቨርሰቲ ሀገሪቱ በምትፈልገው የዕድገት ጎዳና እንድትጓዝ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት ጠንክረው እየሰሩ መሆናቸው ዶክተር ንጉሴ አመልክ

Hailemariam Fires Justice Minister

Image
Hailemariam Fires Justice Minister Justice Minister Brehan Hailu has been fired from his job on Friday, May 10, 2013, reliable sources disclosed to Fortune. Brehan has received a letter from the Prime Minister's Office, signed by Hailemariam Desalegn, late on Friday, according to these sources. Brehan has been serving in this capacity since 2005. He was moved to Justice after his previous ministry, Ministry of Information, was dissolved by law. However, the decision to remove the Minister from Office has come as little surprise in the government circle. He has lost his position in the powerful executive committee of the ruling EPRDF, when elections were held back in March 2013. He was under fire during a convention of his party, the Amhara National Democratic Movement (ANDM), held in Bahir Dar in March, held as a prelude to the EPRDF congress, which was held in the same city. Seconded by a member to the central committee seat in the ANDM, Brehan was harshly criticized by th

Ethiopians want freedom of #Demonstration4every1

Image
Ethiopians on Twitter have started a campaign to demand the right to peaceful protest. Using the hashtags #Demonstration4Every1 and #Assembly4Every1 , a group of online activists are calling on their government to respect an article in Ethiopia's constitution guaranteeing freedom of assembly for citizens.   According to human rights groups, the Ethiopian government has led a crackdown on political protests since declaring a state of emergency after the 2005 elections. There have also been accounts of media censorship, including reports that Al Jazeera's English and Arabic websites have been blocked since July 2012. http://stream.aljazeera.com/story/201305102100-0022747

Ethiopian Journalists Hope New Council Will Ease Restrictions

Addis Ababa — Several Ethiopian publications are coming together to set up a 'press council' with the hope of easing restrictions on the media in Ethiopia. The journalists suggested the idea of the council at a May 3 meeting held at the behest of the Ministry of Information to discuss media reforms in the country. "The meeting was the first time we have had such a direct and open dialogue with the government over press issues," Getachew Worku, editor of the independent publication Ethio Mihidar, told IPS. "We have to welcome this development as a positive step to ease press restrictions." The press council will be formed by editors of government and independent publications. The purpose of the council is to hold discussions about press restrictions and foster direct and frequent dialogue with the government over such issues. Worku said there were still many obstacles for the press to operate freely in Ethiopia. He said, for example, that

Boot Coffee » Lunchtime in Aleta Wondo

Image
Boot Coffee » Lunchtime in Aleta Wondo New

Sidama - Religion and Beliefs

Image
Photo by http://commonriver.files.wordpress.com/2013/01/sr-under-tree1.jpg Introduction to Sidama Religion by Kifle WANSAMO (culled from www.sidamaconcern.com/country/religion_and_beliefs.htm )   1. Introduction 2. Elements of faith in the Sidama religion Belief in God Belief in spirits Belief in ancestors 3. The elements of Response in the Sidama Religion Morality   Prayer & sacrifice Sacrifice Offered to Magano     Sacrifice Offered to the Ancestors   Offering Places 4. Conclusion Endnotes About the author 1. Introduction This paper results from the

የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መደበኛው ስብሰባውን ዛሬ ግንቦት 3/2005 ዓ.ም እያካሄደ ነው፡፡ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በዚሁ ስብሰባው በያዝነው አመት የተሰሩ በክልሎች የከተማና የገጠር ሪፖርት እንዲሁም የገጠር እና የከተማ ሱፐርቪዥን ሪፖርት ላይ ይወያያል፡፡ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በአጀንዳው ከያዛቸው ጉዳዮች መካከል በሚያዝያ ወር በተካሄደው የአዲስ አበባ ምክር ቤትና የአካባቢ ምርጫ አፈጻጸምን በተመለከተ ይመክራል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በ9ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ ላይ የተላለፉ ውሳኔዎችን ወደ አባላት እና ወደ ተለያዩ አካላት ለማድረስና ውሳኔዎቹን ተግባራዊ ለማድረግ በቀጣይ ሁለት አመታት የሚከናወኑ መሰረታዊ ተግባራቶችን ይዳስሳል፡፡ በወቅቱ ከቤቱ በሚነሱ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔዎችን በማሳለፍ ስብሰባውን ያጠቃልላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ምንጭ-የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ምክር ቤት ፅ/ቤት

አመራሩ የኪራይ ሰብሳቢነትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከምንጩ ለይቶ መታገል ይገበዋል-የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር

Image
አዋሳ ግንቦት 01/2005 የኪራይ ስብሳቢነትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከምንጩ በመለየት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አመራሩ መረባረብ እንዳለበት የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አሳሰቡ፡፡ በክልል የሚገኙ ከአንድ ሺህ በላይ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በከተሞች የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የሰራዊት ግንባታ አፈፃፀም ያለበት ሁኔታና ቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ ላይ ለሁለት ቀን ያካሄዱት ውይይት ትናንት ማምሻው ተጠናቋል፡፡ ርዕሰ መስተዳደሩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት በከተሞች የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አንድ በአንድ ለይቶ በማውጣት ለህብረተሰቡ ተገቢውን ምላሽ መስጠት የአመራሩ ቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ በየከተሞች ጎልቶ እየታየ ለመጣው የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በዋናነት ተጠያቂው አመራሩ በመሆኑ እነዚህን ችግሮች ሌት ከቀን በመረባረብ መፍታት እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡ የከተማ ነዋሪዎች ለልማት ስራዎች ያላቸውን ፍላጎትና መነሳሳት አደራጅተውና አቀናጅቶ በመምራት፣ ይህን የልማት አቅም የመጠቀም ውስንነት በአመራሩ ዘንድ በሰፊው የሚታዩ ችግሮች ስለሆነ በፍጥነት ተፈቶ ወደ ስራ መገባት አለበት ብለዋል፡፡ በከተሞች ከዕቅድ ዝግጅት ጀምሮ ያሉ ስራዎችን አንድ በአንድ የመፈተሽ፣ በልማት ሰራዊት የሚሰሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን በየቀኑ የመከታተል፣ እንዲሁም ለስራው ስኬት የሚያግዙ ግብአቶችን በወቅቱ የማቅረብ ጉዳይ ልዩ ትኩረት ተሰቶ ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በከተሞች የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ዓለማ ለማሳካት የዜጎች፣ የባለሙያዎች፣ የባላሃብቶችና የአመራሮች መሰረታዊ የአስተሳሰብ ለውጥ የሚጠይቅ ቢሆንም አመራሩ የመሪነት ሚናውን በተገቢው መንገድ ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ ጠንካራ የልማ

አማራጮች ያልቀረቡበት የዘንድሮ ምርጫ!

“ምርጫዎች ቀን ቆጥረው ይመጣሉ፤ ውጤቱን እንዲለውጡ ግን አንፈልግም” ሶሻሊስቶች ለህዝብ ጥቅም በሚል ሰበብ በሥልጣን ላይ ለመቆየት የሚሹት በዲሞክራሲያዊ መንገድ አይደለም፡፡ በዚህም ሳቢያ ፍትሃዊ ምርጫ ማድረግ አይዋጥላቸውም፡፡ ተፈጥሯዊ ባህርያቸውም አይደለም፡፡ የእነሱ ዝነኛ ብሂል “የትም ፍጪው [ስልጣኑን] አምጭው” የሚል ነው፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ በአገራችን በሚካሄዱ ምርጫዎች፣ ምርጫ ቦርድና አስፈጻሚዎቹ ለምርጫ ሕጎችና አሰራሮች አልፎ ተርፎም ለመርሆዎች ተገዢ አለመሆናቸውና ለጉዳዩ ትኩረት መንፈጋቸው ሳያንስ፣ ገዢው ፓርቲ በገሃድ “ተቃዋሚዎች መጡም አልመጡም ግድ የለንም” እስከማለት መድረሱ ለመድብለ ፓርቲ ስርዓት ፈታኝ ጥያቄ ነው፡፡ የምርጫ ቦርድና የአስፈጻሚዎቹ ትኩረት፣ አማራጭ ሃሳቦች አብብው ሕዝብ በአማራጭ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖረው ማገዝ ሳይሆን እንደ ዓመታዊ በዓል ቀን ቆጥሮ ምርጫውን በማንኛውም ኪሳራ(At any cost) ውስጥ ማስፈፀም እየሆነ የመጣ ይመስላል ፡፡ ይህ አካሄድ የሚጠቁመን ነገር ቢኖር ከጊዜ ወደ ጊዜ ስር እየሰደደ የመጣው ሃቀኛ ዴሞክራሲ ሳይሆን የመንግስታዊ ከበርቴና የልማታዊ መንግስታት አስተሳሰብ መሰረት የሆነው የተምሳሌታዊ ዴሞክራሲ መሆኑን ነው፡፡ መጀመርያ ተቃዋሚዎችን ከነአቤቱታቸው በማስወገድ፣ ቀጥሎ በምርጫው አካሄድና ወግ አልባነት የተቆጣውን መራጭ ሕዝብ፣ ከቁጣው ለማብረድና እምነቱን በተጽእኖ ለማስለወጥ፣ ቤት ለቤት በሚያደርጉት መጠነ ሰፊ ፕሮፓጋንዳና ወከባ ማስጨነቃቸው፣ የፈለጉት የሕዝቡን “የይስሙላ ተሳትፎ” እንጂ ውጤት የማስለወጥ ሕጋዊ መብቱን እንዳልሆነ አይተናል፡፡ ልማታዊ መንግስታት፣ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የመሸነፍና የለውጥ ጥያቄ እንዲነሳባቸው አይፈቅዱም፡፡ ለዚህ ሲባልም የምርጫ ውድድር ቀንን ጠብቆ ምርጫ