Posts

ኢሕአዴግ ቆራጥና ደፋር የውስጥ ትግል ያስፈልገዋል

Image
ኢሕአዴግ በሕዝብ ተከብሮና ተደግፎ ጠንካራ መሠረት ይዞ ለመቀጠል ከፈለገ ይችላል፡፡ የሚችለው ግን ራሱን ሲያጠናክር ነው፡፡ ራሱን ማጠናከር የሚችለው ደግሞ ውስጡን ሲያፀዳ ነው፡፡ ውስጡን ማፅዳት የሚችለው ደግሞ ቆራጥና ደፋር የውስጥ ትግል ሲያካሂድ ነው፡፡ ደፋርና ቆራጥ የውስጥ ትግል ካካሄደ ፀድቶና ተጠናክሮ ይወጣል፣ ይቀጥላል፣ ይጓዛል፡፡ የለም አላደርግም፣ አልታገልም፣ አልቆርጥም፣ አልደፍርም ካለ ደግሞ ውስጥ ለውስጥ እየተሰነጣጠቀ፣ እየበሰበሰና እየተደረመሰ ይሄዳል፡፡ ይደክማል ከሕዝብ ይርቃል፡፡ የነበረው እንዳልነበረ ይሆናል፡፡ ኢሕአዴግ ቆራጥና ደፋር የውስጥ ትግል የሚያስፈልገው ለምንድን ነው? 1.    ከላይ እስከታች በሙስና የተጨማለቁ በዝተዋል! አዎን ንፁኃን የሕዝብ አገልጋይ፣ ለልማትና ለለውጥ የቆሙና የሚታገሉ አባላትም አመራርም በኢሕአዴግ ውስጥ አሉ፡፡ በዚያው አንፃር ደግሞ ከሕዝባዊ መስመር እየራቁና እየሸሹ ለግል ገንዘብ፣ ንብረት፣ ክብርና ኔትዎርክ የሚሯሯጡ፣ በጉቦ የተጨማለቁና በሙስና የተነከሩ አሉ፡፡ እነዚህ በውስጥ ትግል፣ በደፋርና በቆራጥ ትግል ካልተገለሉና ድርጅቱ ካልፀዳ ድርጅቱን እያበሰበሱ የሚገድሉት ናቸው፡፡ 2.    አቅም አልባ… ምላስ  ብዙ በዙ! በብቃት መመደብ እየቀረ ደጋፊ እስከሆነ ችግር የለም እየተባለ የተሾመው ሁሉ የድርጅቱን ዓላማ ማራመድ አልቻለም፡፡ ሕዝቡንም ማገልገል አልቻለም፡፡ ባለአቅም እየጠፋ ባለምላስ በዛ፡፡ ተንዛዛ በጣም በዙ፡፡ ሕዝብ ይህንን እያየና እያስተዋለ ምንድን ነው ነገሩ? እያለ ነው፡፡ አይወስኑም፣ ቢሮ አይገቡም፣ አያሳምኑም፡፡ አንዳንዶቹም ይህን እያወቁ ሀቅን ከመጋፈጥ ይልቅ ሽሽትና ድብብቆሽ እየመረጡ ናቸው፡፡ ሕዝብ በድርጅቱ ላይ አመኔታ እንዲያጣ እያደረጉ ናቸው፡፡ 3.    ጠንካራ አን

Beyond the Politics: - A look at a Reality of Sidama Economy

Image
By Kinkino Kiya, October 25, 2012 According to the most recent World Bank’s report that analysis the World poverty index; Ethiopia by all measures remains one of the poorest countries of the world. The most critical challenge facing the Sidama authorities and the Ethiopian policy makers at large -today and for the years ahead is the urgent task of reducing absolute poverty from the Sidama region as well as for the federal authorities addressing the issues at a national level. The basic objective of economic resources management and the fundamental goal of government anywhere, at all times must be working towards improving the standard of living of their respective people’s over time in the given periods of time. [...] The numerous Ethiopians including the Sidama nation were so optimistic trusting that the current might declare war on the greatest enemy of our people, the abject poverty that has incarcerated the nation of the country with varying degrees. Regardless of the a

ድህነትን ታሪክ ለማድረግ የተቀናጀ ዘመቻ

Image
ተስፋዬ ለማ ከዛሬ አራት ቀን በፊት ማለትም ጥቅምት 2/2005 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አጀንዳ አምድ በዚሁ ርዕስ ከታላላቅ የሀገራችን ልማት ሥራዎች የስኳር ልማት ፕሮጀክት እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረ ጽሑፍ ማቅረባችን ይታወሳል። በጽሑፉ በአገራችን በመስፋፋትና በመገንባት ላይ ያሉ ነባርና አዳዲስ የስኳር ልማት ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያ የምትመራ በትን የግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለማሸጋገር የሚያስችል መሠረት ለመጣል ከተያዙ ታላላቅ ሀገራዊ የኢንዱስትሪ ልማቶች በዋናነት የሚጠቀሱ መሆኑን ዳስሰናል።  በአምስት ዓመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መሠረት ነባሮቹን የማስፋፋትና አዳዲሶች የመገንባት አቅጣጫ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን ለማየትም ተሞክሯል። ከእዚሁ ጋር ተያይዞ የአገሪቱ የስኳር ፍላጎት ከሚመረተው ምርት ጋር ባለመጣጣሙ መንግሥት ከተለያዩ አገራት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ስኳር እያስገባ መሆኑን ጠቁመን ከሦስት ዓመታት በኋላ ግን አገሪቱ የሕዝቧን የስኳር ፍላጎት አሟልታ የተረፈውን ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተሻለ የውጭ ምንዛሪ የምታስገባበት ሁኔታ እንደሚፈጠር አይተናል።  ከስኳር ልማት ፕሮጀክቶቹ ጋር ተያይዞ በተለያዩ ወገኖች የሚነሱ መሠረት የለሽ አሉታዊ ዘገባዎች የአገራችንን የልማት አቅጣጫ ለማስቀየስ እንጂ መሠረታዊ ጠቀሜታ ኖሯቸው እንዳልሆነና በአሁኑ ወቅት ልማታችንን ለማደናቀፍ የሚሰነዘሩ አሉባልታዎችን የሚሰማ ጆሮ ያለው ኢትዮጵያዊ አለመኖሩንም ለማስገንዘብ ተሞክሯል። የኢትዮ ጵያ ሕዝብ ዋነኛ ጠላት ድህነት መሆኑን መግባ ባት ላይ መደረሱንም ነው በመጀመሪያው ጽሑፍ የቃኘነው።  በዛሬው ጽሑፍ በሀገራችን እየተገነቡ ካሉ አዳዲስ የስኳር ልማት ፕሮጀክቶች የወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክትን እንመለከታለን።  የወልቃይ

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የቡና ጉባኤ ሊካሄድ ነው ለውጭ ገበያ ከሚቀርበው ቡና 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ እንደሚገኝ ይጠበቃል

Image
አዲስ አበባ ጥቅምት 16/2005 በቡና ንግድ ዘርፍ መላው ባለድርሻ አካላትን የሚያሳትፍ የመጀመሪያው ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ በቅርቡ አዲስ አበባ ውስጥ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ኮፊ ኤክስፖትርስ አሶሴሽን አስታወቀ፡፡ ኢትዮጵያ ዘንድሮ ለዓለም አቀፉ ገበያ ከምታቀርበው የቡና ምርት 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ እንደምታገኝ ይጠበቃል፡፡ የአሶስዬሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ኦፊሰር አቶ ጌታቸው አድማሱ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጸው ጉባኤው የቡና ምርቶች መገኛ የሆነችውን ኢትዮጵያን ገጽታን ከመገንባት ባሻገር የተለያዩ ምርቶቿን ለዓለም አቀፉ ገበያ ለማስተዋወቅ የሚረዳ ነው፡፡ አሶስዬሽኑ ጉባኤውን በሚቀጥለው ሳምንት በአዲስ አበባ ሒልተን ለማካሄድ ከንግድ ሚኒስቴርና ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑንና በአሁኑ ወቅትም አስፈላጊውን ቅድም ዝግጅት በማጠናቀቅ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ለሁለት ተከታታይ ቀና በሚካሄደው ዓለም ዓቀፍ የቡና ጉባኤም 250 ሰዎች እንደሚሳተፉ ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ ጌታቸው ገለጻ ከአገር ውስጥ በቡና ንግድ የተሰማሩ ላኪዎችና አቅራቢዎች ድርጅቶች፣ የሕብረት ስራ ማህበራት ዩኒየኖችና የክልል ግብርና ቢሮ ተወካዮች፣ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅት ተጠሪዎችና የገንዘብ ተቋማት ይሳተፋሉ፡፡ በተጨማሪም ከውጭ ዓለም ዓቀፍ የቡና ገዢዎች፣ ቆይና ቸርቻሪዎች የጉባኤው እድምተኞች ይሆናሉ፡፡ በጉባኤውም በተለይ በቀጣዩ አውሮፓውያን ዓመት የኢትዮጵያ ቡና ምርት የውጭ ገበያ አቅርቦት በሚያድግበት እንዲሁም አገሪቱ ከዘርፉ የምታገኝው የውጭ ምንዛሪ ገቢም በዚያው ልክ የሚጨምርበት ሁኔታ በመምከር አዎታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ በዓለም ዓቀፉ ገበያ የኢትዮጵያ የቡና ወጪ ንግድ አቅርቦት አሁን ካለበት መጠ

1433ኛው የዒድ አል አድሃ አረፋ በዓል ዛሬ እየተከበረ ነው

Image
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) 1ሺህ 433 ኛው የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ ነው ። ከስያሜው ጀምሮ ከነቢያት አባት ከኢብራሂም አሌሂሰላም ታሪክ ጋር ቀጥተኛ ተዛምዶ ያለው የአረፋ በዓል ፥ የእምነቱ ተከታዮች ዘንድ የእርሳቸውን ታሪክ በማስታወስ ለሰው ልጅ ደህንነት የከፈሉትን መስዋዕትነት በየዓመቱ የሚዘክሩበት በዓል ነው ። በቅዱስ ቁርአን እንደመለከተው ነብዩ ኢብራሂም ልጃቸው እስማኤልን በአላህ ትእዛዝ ለመስዋት ሲያዘጋጁ ፤ በምትኩ ሙክት በግ መስዋት መቅረቡን ያሳያል በዚህም ኢድ አል አድሃ የመስዋት በዓል ተብሎ ይከበራል። በዓሉ ኢድ አልአድሃ ተብሎ የሚከበረውም ኡዲሂያ ወይም መስዋዕት ስለሚታረድ መሆኑን ፥ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ አህመዲን ሼህ አብዱላሂ ጨሎ ይናገራሉ። በዚህ ታላቅ ሃይማኖታዊ ቀን እርስ በርስ መዘያየርና ደስታን መገላለጽ በፈጣሪ ዘንድ በእጅጉ የሚወደድ ተግባር ነውና ከሁሉም ይህ ይጠበቃል። በአሉ ሲከበርም ሁሉም የእምነቱ ተከታይ በዓሉን በደስታ ያከብር ዘንድ ያለው ለሌለው መዘየር ዋነኛ ተግባር ይሆናል። በኢድ ቀን ከሚፈጸሙት ኢባዳዎች አንዱ ኡዲሂያ ሲሆን ፥ ለኡሂዲያ ከሚታረደው ከብት መካከል ለጎረቤትና ለተቸገሩ ማጋራት የእምነቱ ስርዓት ያዛል። የበአሉ አካል የሆነው የስግደት ስነ ስርዓት /ሶላት/ ማለዳ 1 ሰዓት ከ30 ላይ በጋራ በየአካባቢው እየተካሄደ  ሲሆን ፥ በመዲናችን አዲስ አበባም የሶላት ስነ ስርዓቱ በአዲስ አበባ ስታዲየም እየተፈጸመ ይገኛል ።  የበአሉ አካል የሆነው የስግደት ስነስርዓት /ሶላት/ ማለዳ ላይ በጋራ በየአካባቢው የተካሄደ  ሲሆን ፥በመዲናችን አዲስ አበባም የሶላት ስነስርዓቱ በአዲስ አበባ ስታዲየም በ

የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ለአቶ መለስ መታሰቢያነት እንዲውል ተወሰነ

Image
የዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ መታሰቢያነት በማዋል እንዲከበር መወሰኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስታወቀ፡፡ እንደ ዋልታ ዘገባ፣ ከመጪው ኅዳር ወር መጀመርያ አንስቶ ለአንድ ወር በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በየደረጃው የሚከበረው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ክብረ በዓል መታሰቢያነቱ በሞት ለተለዩት አቶ መለስ እንዲሆን የወሰነው ምክር ቤቱ ነው፡፡ ምክር ቤቱ ይህን የወሰነው ባለራዕዩ መሪ ለኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች እኩልነት አብዛኛውን ዕድሜያቸውን በፅናት የታገሉለት ዓላማ ስለነበር ነው መባሉን ዘገባው አስረድቷል፡፡ የዘንድሮ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን “ብዙም አንድም ሆነን የታላቁ መሪ ራዕይ በሕገ መንግሥታችን ለህዳሴያችን” በሚል መሪ ቃል እንደሚከበር ተጠቁሞ፣ ከመጪው ወር መጀመርያ ጀምሮ በአገሪቱ ሁሉም ቀበሌዎች ውይይት እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡ በብሔራዊ ደረጃ ኅዳር 29 ቀን በባህር ዳር ከተማ በዓሉን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ከወዲሁ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ዘገባው አመልክቷል፡፡

“መልካም አስተዳደርን ያላካተተ ልማት ልማት አይባልም”

በምሕረት ሞገስ ኢትዮጵያ በልማቱ ዘርፍ የኢኮኖሚ ዕድገት ታስመዝግብ እንጂ ዴሞክራሲን በማስፈን ወደኋላ እንደቀረች የተለያዩ የሰብአዊ መብትተሟጋች ሪፖርቶች ያሳያሉ፡፡ ኢሕአዴግም ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ አንሥቶ ትችት ሲሰነዘርበት የቆየው ዴሞክራሲን ማስፈን ባለመቻሉ ነው፡፡ መንግሥት ዴሞክራሲን ለማስፈን ብዙ ትኩረት ባለመስጠቱ የበላይና የበታች እንዲኖር፣ ፍትሕ እንዲዛባ በአጠቃላይም የመልካም አስተዳደር እጦት በአገሪቷ እንዲስፋፋ አድርጓል በሚልም ይተቻል፡፡  አቶ አሰፋ አደፍርስ በአሜሪካ ለ39 ዓመታት ኖረዋል፡፡ በኢትዮጵያ በልማቱ ዘርፍ ከተሰማሩም ዓመታትን አስቆጥረዋል፡፡ በሥራ አጋጣሚ የሚያስተውሉት የመልካም አስተዳደር እጦት ግን አገሪቷን ወደኋላ የጐተተ፤ እሳቸውና ሌሎች ባለሃብቶችም የተሰማሩባቸውን የተለያዩ የልማት ዘርፎች ከሚፈለገው ደረጃ እንዳይደርስ ማነቆ የሆነ ችግር እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡ የመልካም አስተዳደር እጦት በተንሰራፋበት ሁኔታ የሚታይ የኢኮኖሚ ዕድገትም በሕዝቡ ኑሮ ላይ ለውጥ እንደማያመጣም ይናገራሉ፡፡ ከሚኖሩበት አሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ በአገሪቱ ለውጥ ማየታቸውን፤ ሆኖም ለውጡ መሳጭ አለመሆኑን የሚናገሩት አቶ አሰፋ “አገር ውስጥ ያለውም ሆነ ከውጭ የሚመጣ ባለሀብት ሕንጻ ሊሠራ ይችላል፡፡ ሕንጻ ስለተደረደረ ግን ልማት ለማ ማለት አይደለም፡፡ አገራችን ኢትዮጵያ ከሕዝቧ በላይ ሊያስተዳድር የሚችል ሀብት አላት፡፡ ሆኖም በየመንገዱ የሚለምን እናያለን፣ ልጃቸውን አዝለው የሚበሉት የሚጠይቁ ይታያሉ፡፡ ይህ የሚሆነው ከመልካም አስተዳደር እጦት በሚመነጭ ችግር ነው፡፡ መልካም አስተዳደርን ያላካተተ ልማት ልማት አይባልም፤” ብለዋል፡፡ በመልካም አስተዳደር እጦት ላይ ያለው ችግር አሁን የመጣ ሳይሆን የቆየ ሊሆን ይችላል፡፡ በደርግ ጊዜ ከነበረው ጋ

In Retrospect..

ከማህበራዊ መረብ የተገኘ ጽሁፍ  In Memory of the two precious sidama children shot by police last june in Chuko woreda demonstrating for the causes of the entire sidama people; This last summer has witnessed many glaring events in the history of sidama nation. Provoked by the state's move to federalise the Hawassa city thereby diminishing the strongholds of power of sidama people, this peaceful land has evidenc ed historic accomplishments and failure in various times and places. The two entirely divergent philosophies of the gov't and the people as to the issue at hand make the situation and any harmonizing attempt fruitless, resulting in wholesale adversity b/n the people and the state. Being anxious and disguised by this very gov't orientation, the people determined to call for regional self-determination, claiming that these all atrocities are pressing on the people due to lack of such a status like other comparable nations in the Ethiopian polity. This endless struggle resulted

Animal Tales from Sidama

Image
Please! write reviews

Traditional Sidama Tales

Image
link

በደቡብ ክልል በ2ዐዐ4 ዓ/ም በሁሉም ዘርፎች ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የደኢህዴን ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

የደኢህዴን ከፍተኛ አመራሮች እያካሄዱ ባሉት 6ኛ ቀን የግምገማና የስልጠና መድረክ ላይ ያለፈው ዓመት በርካታ ተግባራት የተከናወነበት ዓመት መሆኑን ገምግሟል፡፡ በግብርናው ዘርፍ በተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት ውስጥ በከፋ ዞን የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተደረገው ጥረት ከ75 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኝ መተከሉን በአብነት አንስቷል፡፡ በሰብል ምርትና ምርታማነት ረገድ በክልሉ ማዕከላዊ ዞኖች ውስጥ በስልጤ፣ በሀድያ፣ በከምባታ ጠምባሮና በወላይታ ዞኖች ውስጥ ከፍተኛ የሰብል ምርት እድገት መመዝገቡ ተገልጿል፡፡ በመሆኑም ድርጅቱ ባካሄደው የ2ዐዐ4 ዓ/ም አፈፅፀም የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራትን በማስቀጠል የአቶ መለስ ዜናዊን ራዕይ በማሳካት የህዳሴ ጉዞን እውን ማድረግ በሚቻልበት ቁመና ላይ መድረሱንም ገልጿል፡፡ባልደረባችን ታሪኩ ለገሰ ዘግቧል፡፡ ማህበራቱ ውጤታማ እንዲሆኑና የቁጠባ ባህላቸውን እንዲያሳድጉ በወጪና ገቢ አያያዝ ላይ ስልጠና  እንደሚሰጥም ተናግረዋል፡፡ ሳሙኤል መንታሞ ከወልቂጤ ቅርንጫፍ እንደዘገበው፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/14TikTextN405.html

የዴሞክራሲ ስርዓትና መልካም አስተዳደር ለመገንባት የህግ የበላይነት መረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡

የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በክልሉ ለሚገኙ ዳኞች በወንጀለ ቅጣት አወሳሰን በግሙሩክና በታክስ ጉዳዮች የእስራት ቅጣት ዙሪያ በቡታጅራ ከተማ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡          የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ኘሬዝዳንት አቶ ታረቀኝ አበራ እንደተናገሩት መልካም አስተዳደር ለመገንባትና ልማትን ለማፋጠን እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን ለማስቀጠል በህግ የበላይነት ላይ የተመሰረተ የፍትህ አሰጣጥ እንዲኖር የቅጣት አወሳሰን ወጥና ትክክለኛ መሆን አለበት፡፡ በወንጀል ፍትህ ስርዓት ውጤታማነትና ፍትሀዊነትን በማረጋገጥ ስራ ላይ ከዚህ በፊት የተለያዩ ችግሮች ይታዩ እንደነበር የጠቆሙት ኘሬዝዳንቱ ችግሩን ለመቅረፍ በቅጣት አወሳሰን ላይ ተቀራራቢ የሆነ የቅጣት አወሳሰን እንዲኖር እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ስልጠናው ሁሉም ዳኞች በተገቢው እውቀት ቅጣት አወሳሰድ ላይ ወጥ የሆነ ሥራ  እንዲሰሩ የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በስልጠናቸው ከክልሉ የተውጣጡ የዞኑ የወረዳ የፍርድ ቤት ኘሬዝዳንቶች እንዲሁም ዳኞች ተሳታፊ ሆነዋል ሲል የጠቅላይ ፍርድ ቤት የመንግሰት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዘግቧል፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/13TikTextN105.html

ከ2ዐዐ2 ዓ/ም ጀምሮ በደቡብ ክልል ምክር ቤት አባልነት ሲያገለግሉ የቆዩት የተከበሩ አቶ ሀይሌ ባልቻ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ፡፡

ክቡር አቶ ኃይሌ ባልቻ ከወጣትነት እድሜያቸው ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማዎች የተመራውን ፀረ ፊውዳላዊ ተቃውሞ በወቅቱ የነበሩ የይርጋዓለም ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችም በትግል አጋርነት እንዲቀላቀሉ አስተባባሪ በመሆን መርተዋል፡፡ ክቡር አቶ ሀይሌ ባልቻ በደርግ ዘመን በ1997 ዓ/ም በተካሄደው ብሔራዊ ሸንጎ ምርጫ በጎርቼ ምርጫ ክልል በእጩነት ቀርበው የደርግ ሥርዓት እስከ ተወገደበት እስከ 1983 ዓ/ም ድረስ የመርጣቸው ህዝብ መብት መከበር የበኩላቸውን ድርሻ ማበርከታቸውን የህይወት ታሪካቸው ይገልፃል፡፡ በማህበሪዊ ህይወታቸውም የስኳር በሽታ ህሙማን የሆኑና ከፍለው መታከም የማይችሉ የሀዋሣና የአካባቢው ታማሚዎችን በማስተባበር የስኳር ህሙማን ማህበር በማቋቋም የህክምና እርዳታና ስለ በሽታው ግንዛቤ እንዲያገኙ በጎ ተግባርን ፈፅመዋል፡፡ በቤተሰብ ህይወታቸውም ሴት ልጅን በማስተማር በአካባቢው ህብረተሰብ ዘንድ እንደ መልካም አርአያ ይቆጠሩ አንደነበር የህይወት ታሪካቸው ያመለክታል፡፡ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ጥቅምት 12/2ዐዐ5  ሲፈፀም ሥነ ሥርዓቱ ላይ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ጨምሮ የከልል፣ የሲዳማ ዞንና የሀዋሣ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ባለስልጣናት እንዲሁም ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል፡፡ ክቡር አቶ ሀይሌ ባልቻ ባለትዳርና የ6 ወንድና የ4 ሴት ልጆች አባት ነበሩ፡፡ የዞኑ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች እንደዘገበው፡፡

መምህራንን ለመመዘን ዝግጅቱ ተጠናቅቋል

Image
ሃዋሳ፡- የመምህራንን የሙያ ምዘና ለማካሄድ ዝግጅት መጠናቀቁን ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ። የመጀመሪያው የመምህራን ምዘና በሕዳር 2005 መጨረሻ እንደሚካሄድ አስታወቀ። የደቡብ ክልል 18ኛ አጠቃላይ የትምህርት ጉባዔ ሰሞኑን በሃዋሳ ከተማ ሲዳማ ባህል አዳራሽ በተካሄደበት ወቅት በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራን ሙያ ፈቃድ አሠጣጥና እድሳት ዳይሬክተር አቶ ሳህሉ ባይሳ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት የመምህራንን የሙያ ምዘና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማካሄድ በመንግሥት በኩል ዋና ዋና ዝግጅቶች ተጠናቅ ቀዋል። ለምዘና ሥራው የሚረዱ ስታንዳርዶችን የማውጣትና እነዚህን ለማስፈፀም የሚረዱ መመሪያዎችን የማዘጋጀቱ ሥራ መጠናቀቁን የገለጹት አቶ ሳህሉ፤ ለምዘና ሥራው አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁስ መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል። የፈተናው ዝግጅት ሥራም በትምህርት ሚኒስቴር በኩል እየተከናወነ መሆኑንና በተያዘው ዓመት መጀመሪያ ተጨባጭ ተግባራት ለመጀመር መታቀዱን አብራርተዋል። በአገራችን የመምህራን ሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት ሥርዓት ሲጀመር ይህ የመጀመሪያው እንደሚሆን አቶ ሳህሉ ገልጸው፤ የመምህራን ምዘና ለትምህርት ጥራት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመዋል። መምህራን በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ መሠረት ሙያቸውን እየፈፀሙ መሆኑን ለማወቅ እንደሚያስችልም ተናግረዋል። የምዘና ሥራው በዋናነት በክልሎች እንደሚመራ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ ትምህርት ሚኒስቴር ስታንዳርዶችንና መመሪያዎችን የማውጣትና የምዘና ሥራውን በበላይነት የመቆጣጠር ሥራ እንደሚያከናውን አስረድተዋል። በቅርቡ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠው ፈተና በትምህርት ሚኒስቴር እንደሚዘጋጅና በቀጣይ ፈተናው በክልሎች የሚዘጋጅ መሆኑንም አስረድተዋል። ፈተናውን የመምራትና የማስተዳደር ኃላፊነትም የክልሎች እንደሚሆን አስታውቀዋል።

Judge Firehiwot Samuel's testimony on Prime Minister Hailemariam Desalegn

Image
Judge Firehiwot Samuel's testimony on Prime Minister Hailemariam Desalegn

በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ሕፃናት ዓለም አቀፍ የጉዲፈቻ አገልግሎት ተጠቃሚ ይሆናሉ

Image
ሃዋሳ፡- በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙና አማራጭ የሌላቸውን ሕፃናት በሀገሮች መካከል በሚደረግ የጉዲፈቻ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ሚኒስቴር እየሠራ መሆኑን ገለጸ። በሀገሮች መካከል የሚደረገውን የጉዲፈቻ አገልግሎት ለማስፈፀም በወጣው የሄግ ስምምነት የአፈፃፀም ሂደት ላይ የባለድርሻ አካላትን አቅም ለማጎልበት በሀዋሳ ከተማ በተካሄደው የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ላይ የሚኒስቴሩ የሕፃናት መብትና ደህንነት የማስጠበቅ ዳይሬክተር ወይዘሮ ያየሽ ተስፋሁኔ እንደተናገሩት፤ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙና አማራጭ የሌላቸው ሕፃናት በሀገሮች መካከል በሚደረግ የጉዲፈቻ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው። በሀገሮች መካከል የሚደረግን የጉዲፈቻ አገልግሎት ለማስፈፀም በወጣው የሄግ ስምምነት ሰነድ ላይ የተቀመጡ ሕጎችና አሠራሮችን እንዲሁም ኮንቬንሽኑን ለማስተግበር መዘጋጀቱን የገለጹት ዳይሬክተሯ፤ በማዕከላዊ ደረጃ በሚዋቀረው ተቋምና በአሠራሮቹ ዙሪያ የባለድርሻ አካላትን ግንዛቤ ለማስፋት መድረኩ ምቹ መሠረት እንደሚጥል ተናግረዋል። ኮንቬንሽኑን ተግባራዊ ለማድረግ የመንግሥት አካላት ከልማት አጋሮች ጋር በተቀናጀ በበቂ ግንዛቤ ላይ የተመሠረተ ሥራ መሥራት ይጠበቅብናል። ሕፃናት በሁሉም ረገድ የሚገጥማቸውን ችግሮች በተቀናጀ መልኩ ለመፍታትና ሁለንተናዊ መብታቸውንና ደህነነታቸውን በተጨባጭ ለማስከበር የሚደረገውን ሀገራዊ እንቅስቃሴ ወደ ላቀ ደረጃ ከማሸጋገር አኳያ መድረኩ በተሻለ አቅም እንደሚሠራ ተናግረዋል። ውይይቱ በፌዴራልና በክልል የመንግሥት አስፈፃሚ አካላት መካከል ቅንጅታዊ አሠራርን ከማጠናከር አኳያ ፋይዳው ጉልህና ውጤታማ እንደሆነም አብራርተዋል። በሕፃናት ሰብአዊ መብት መ

በሲዳማ ዞን ባፈው የክረምት ወራት ከ111 ሺህ በላይ ወጣቶች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት...፡

በሲዳማ ዞን ባፈው የክረምት ወራት ከ111 ሺህ  በላይ ወጣቶች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመሳተፍ 3 ሚሊዮን የሚጠጋ የመንግስት በጀት ከወጪ ማዳናቸውን የዞኑ ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የወጣቶች ዘርፍ በ2ዐዐ4 እቅድ አፈፃፀምና በ2ዐዐ5 እቅድ ትግበራ ዙሪያ ሰሞኑን ውይይት አካሂደዋል፡፡ በዚህን ወቅት የመምሪያው ምክትልና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዲሱ ሳሙኤል እንዳሉት ወጣቶቹ በተለያዩ የማህበረሰብ ልማት ሥራዎች በመሳተፍ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ አድርገዋል፡፡ በአካባቢ ልማትና በአፈር ጥበቃ ብቻ ከ5 ሺህ 5ዐዐ በላይ ወጣቶች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ በሌላ በኩል በፓኬጅ ለተደራጁ ወጣቶች ከተሰራጨው ከ13 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ የብድር ገንዘብ 6 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር እንዲመለስ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡ ይሁንና አፈፃፀሙ ከግማሽ በታች ነው ያሉት ምክትል ኃላፊው ለዚህም በምክንያነት የሚጠቀሱት የተሰጠው ብድር ሳይመለስ በወቅቱ የነበሩ ኃላፊዎች መቀያየር እንዲሁም አንዳንድ ወጣቶች ገንዘቡ የማይመለስ አድርገው መመልከትና ጉዳዮ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተቀናጅቶ ያለመሥራት ናቸው ብለዋል፡፡ ዘገባው የሲዳማ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ነው፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/9TikTextN405.html

በደቡብ ክልል ከተገነቡ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አብዛኛዎቹ አገልግሎት ጀመሩ

አዋሳ ጥቅምት 14/2005 በደቡብ ክልል በ240 ሚልዮን ብር እየተገነቡ ካሉ 50 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 46ቱ ተጠናቀው አገልግሎት መጀመራቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ፡፡ የቢሮው የመንግስት ኮሙኒኬሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ አዳነ ንጉሴ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በክልሉ የምዕተ ዓመቱን የትምህርት ልማት ግቦች ለማሳካት ለተገነቡት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የውስጥ ድርጅት በማሟላት አገልገሎት ጀምረዋል፡፡ ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልገሎት ከበቁ ትምህርት ቤቶች መካከል 32ቱ ከ9ኛ እስከ 10ኛ ቀሪዎቹ የመሰናዶ ትምህርት ቤቶች ሲሆኑ ግንባታው የአስተዳደር ቢሮ፣ ቤተ ሙከራ፣ ቤተ መፃህፍትና የመፀዳጃ ቤቶችን ያካተተ ነው ብለዋል፡፡ የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ በአብዛኛው የተከናወነው ቀደም ሲል 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች ባልተዳረሰባቸው ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች መሆኑን የገለጹት አቶ አደነ በዚህ አካባቢ የሚታየውን የተሳትፎ ልዩነት ለማሻሻል እንደሚረዳም ተናግረዋል፡፡ ትምህርት ቤቶቹ ለአገልገሎት መብቃታቸው በክልሉ 287 የነበረውን የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ቁጥር ወደ 333 በማሳደግ ከ22ሺህ ለሚበልጡ ተጨማሪ ተማሪዎች የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡ በተለይ ሴቶች የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ከመረዳቱም ባሻገር በትምህርት ቤትና በመኖሪያ አካባቢ መካከል ባለው ርቀት ምክንያት የሚደረሰውን ችግር የሚያስቀርና አቅም የሌላቸው ወላጆችን ችግር በእጅጉ እንደኒፈታ ገልጸዋል፡፡ በ2004 የትምህርት ዘመን አንድ ለ 66 የነበረውን የተማሪ ክፈል ጥምርታን ወደ አንድ ለ 60 ለማድረስ በመቻሉ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡ አዲስ ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁ ትምህር

የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነርና ሁለት የዞን ፖሊስ አዛዦች ታስረው እንዲቀርቡ ታዘዘ የሲዳማ ዞን ፖሊስ መምርያ አዛዥም ይገኝበታል

በታምሩ ጽጌ የፌዴራል ፍርድ ቤት ትዕዛዝን አላከበሩም በሚል የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ወይም ምክትል ኮሚሽነር፣ የጌዲኦ ዞን ፖሊስ መምርያ አዛዥንና የሲዳማ ዞን ፖሊስ መምርያ አዛዥን የፌዴራል ፖሊስ አስሮ የፊታችን ዓርብ እንዲያቀርባቸው የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዘዘ፡፡ ፍርድ ቤቱ ኃላፊዎቹ ታስረው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ያስተላለፈው ምክንያቱ ግልጽ ባልሆነና ባልታወቀ መንገድ ሥራውን እንዲያቆም የተደረገው፣ በጌዴኦ ዞን ይሠራ የነበረው የሳማሪታንስ ፐርስ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት ሠራተኞች ባነሱት የመብት ጥያቄ ጉዳይ መሆኑ ታውቋል፡፡ በድርጅቱ ላይ ክስ መሥርተው ለነበሩት አቶ ደረጀ ገብረ ማርያም፣ ወ/ሮ አቢጊያ ለገሰ፣ አቶ ሰለሞን ሙሉጌታ፣ ወ/ሮ ምህረት አበራ፣ አቶ ዮሐንስ አዳሙ፣ ወ/ሮ እመቤት ዓለሙ፣ አቶ አዲስ አበባና አቶ መስፍን ግዛው፣ የፌዴራል መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት እንደየአገልግሎታቸው እንዲከፈላቸው ያስተላለፈውን ውሳኔ ለማስፈጸም፣ በድርጅቱ አካውንት ውስጥ ምንም ዓይነት ገንዘብ ባለመኖሩ፣ የድርጅቱ ንብረት መሆናቸው የተረጋገጡ ተሽከርካሪዎችን በመያዝና በሐራጅ ተሸጠው እንዲከፈላቸው ታህሳስ 27 ቀን 2003 ዓ.ም. ውሳኔ ማስተላለፉን የውሳኔው ግልባጭ ያስረዳል፡፡ ተሽከርካሪዎቹ ቆመው በተገኙበት የዞኑ ፖሊስ አዛዦች ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች ፍርድ አፈጻጸም መምርያ እንዲያስረክቡ በተደጋጋሚ ትብብራቸውን ቢጠየቁም ሊያቀርቡ ባለመቻላቸውና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን እንዲያስፈጽም ቢታዘዝም ተፈጻሚ ሊያደርግ ባለመቻሉ፣ ሦስቱም በፌዴራል ፖሊስ ታስረው ጥቅምት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ተላልፏል፡፡ የፍርድ ባለመብቶቹ ላለፉት ሁለት ዓመታት ሕግ በወሰነላቸው መብት ተጠቃሚ አለመሆናቸውንና በመጉላላት ላይ እንደሆኑም ፍርድ ቤ

በሲዳማ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር የሬዲዮ ፕሮግራም በቅርቡ ይጀምራል

በሲዳማ ወቅታዊ ጉዳዮ ላይ በተለይ ኢኮኖሚያዊ፤ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት የምያደርገው ''ሲዳማ በዚህ ሳምንት'' የተባለው የኢንተርኔት ላይ ሬዲዮ ፕሮግራም በወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ኣማካይነት በኣለም ላይ ለምገኙ የሲዳማ ተወላጆች እና ሲዳሚኛ ኣድማጮቹ ይስራጫል። የሙከራ ፕሮግራሙን ከታች ይከታተሉ:፡  Click Here የሙከራ ፕሮግራም

2012/13 Premier league “Meles Cup” season kicks-off Saturday

The 2012/13 Ethiopian premier league “Meles Cup” championship brings city rivals Saint George and Ethiopian Coffee in a head-on clash  for the  season’s opening weekend showdown. Runner-up Dedebit FC travels to  Yirgalem to face Sidama Coffeewhile newcomers Water Sport,  in their first-ever premier league match, is set to play against third place Electric FC.   The new season,  dedicated to the late Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi, brings together 14 teams, including newcomers Insurance and Water Sport, for  fixtures to be conducted in two rounds. With eight teams from Addia Ababa, three from SNNPR, two from Oromia and one from Harar in contention, the new season is expected to bring the best out the players and fans,  following the superb triumph that the Ethiopian national team had against its neighbour, Sudan. The discipline and support of the great fans coupled with the determination of our players is something that will not be forgotten in a long time.  Of the fourteen, 

በሲዳማ ዞን የአሮሬሳ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት ሠራተኞች ለህዳሴው ግድብ ለ2ኛ ጊዜ በ1 ወር ደመወዛቸው ቦንድ ለመግዛት መስማማታቸውን ገለጹ፡

የወረዳው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ማሞ እንዳሉት ሠራተኞቹ ለቦንድ ግዥው ደመወዛቸውን የሚቆርጡት ከጥቅምት ወር ጀምሮ ነው፡፡ የወረዳው ደኢህዴን ን/ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጋቢሶ ጋቢባ በበኩላቸው በትምህርት ጥራት ላይ ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት ህዝቡ፣ መንግሥትና ድርጅት የአንድ ዓላማ የልማት ሠራዊት ሆነው መሥራት አንዳለባቸው አመልክተዋል፡፡ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጉሴ ዎራና ትምህርት ቤቶችን ቁጥር 53 በማድረስ በትምህርት ተደራሽነት ላይ የተገኘውን ስኬት በትምህርት ጥራትም ላይ መድገም አለብን ብለዋል፡፡ ዘገባው የሲዳማ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን  መምሪያ ነው፡፡

በተያዘው የበጀት አመት በሽታን በመከላከልና ጤናን በማጎልበት የህክምና አገልግሎቶችን በጥራትና በፍትሀዊነት ለህብረተሰቡ ለማዳረስ አቅዶ እየሰራ መሆኑን በሲዳማ ዞን የጎርቼ ወረዳ ጤና አጠባበቅ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

የወረዳው ጤና አጠባበቅ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ተረፈ ያዕቆብ እንደገለፁት በወረዳው በጤናው ዘርፍ የሚሰጡትን አገልግሎቶች ተደራሽነት ለማረጋገጥ የጤና አገልግሎት ተቋማትን በየቀበሌው በማስፋፋትና የጤና ልማት ሠራዊትን በመገንባት በተያዘው የበጀት ዓመት በዘርፉ ሰፊ ስራ ለመስራት ታቅዷል፡፡ በወረዳው ባለፈው የበጀት ዓመት የእናቶችንና የህፃናትን ጤና በመንከባከብ ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር እንዲያስችል የፀረ ዘጠኝና የፖሊዬ ክትባቶች ተደራሽነት በበቂ ሁኔታ መከናወኑን ኃላፊው ገልፀው ከዚህም የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በመቀመር በዘንድሮው ዓመትም የተሻለ አፈፃፀም ይመዘገባል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በወረዳው የሚገኙ የተለያዩ የህብረተሰብ አደረጃጀቶችንና ከ5መቶ 30 በላይ ቁርኝቶችን በመጠቀም አስራ ስድስቱን የጤና ኤክስቴንሽን ፖኬጆችን ለመተግበር በ6 የጤና አጠባበቅ ጣቢያዎችና በ21 ጤና ኬላዎች ህብረተሰብ አቀፍ የጤና ስራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙም ገልፀዋል፡፡ አምባዬ አዳነ ከበንሳ ቅርንጫፍ እንደዘገበው፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/6TikTextN305.html

የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ስለምርጫ ሥነ ምግባር አዋጁና ድርድር ምን ይላሉ?

‹‹የሥነ ምግባር አዋጁን ፈርመን ብንደራደር በግሌ ችግር የለብኝም›› አቶ ግርማ ሰይፉ (መድረክ) ‹‹እንደ ዜጋ አዋጁን አከብራለሁ አስገድደው ሊያስፈርሙን ግን አይችሉም›› ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ (መድረክ) ‹‹አጠቃላይ መፍትሔ አምጪ ባይሆንም አንድ ዕርምጃ ነው›› አቶ ሙሼ ሰሙ (ኢዴፓ) ‹‹አዋጁን ፈርመን ብንቀበልም ያስከበረልን ነገር ስለሌለ ከጋራ መድረክ ወጥተናል›› አቶ ወንድማገኝ ደነቀ (መኢአድ) በዮሐንስ አንበርብር የፓርቲዎች የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ የበርካታ ፓርቲዎች ይሁንታን አግኝቶ ከፀደቀ ሦስት ዓመታት ያለፉት ቢሆንም፣ ይህ የሥነ ምግባር አዋጅ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ሒደት ውስጥ ካበረከተው አስተዋጽኦ ይልቅ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ፈተና የሆነ ይመስላል፡፡ አንዳንዶቹ በአዋጁ ዙሪያ እርስ በእርስ አይግባቡም፤ ሌሎች ደግሞ አዋጁን ፈርመን የገባንበት የድርድር መድረክ ያመጣልን ነገር የለም ይላሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ በተቋቋመው የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተሳታፊ መሆናቸውን ይገልጻሉ፡፡ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥታቸውን አቋም ባለፈው ማክሰኞ ያቀረቡት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ ከመድረክ ፓርቲ ለቀረበላቸው የድርድር ጥያቄ የኢሕአዴግንና የሚመሩትን መንግሥት አቋም አሳውቀዋል፡፡ መድረክ ከኢሕአዴግ ጋር ለመወያየት በመጀመሪያ የሥነ ምግባር አዋጁን መፈረም አለበት፡፡ ይህ ካልሆነ ግን የውይይት መድረኩ የተዘጋ ነው ማለታቸው ይታወሳል፡፡ ይህንን አስመልክቶ የመድረክ አመራሮችን ያነጋገርን ሲሆን፣ መድረክ በተሰጠው ምላሽ ላይ ተነጋግሮ አቋም ያለመያዙን ለመረዳት ተችሏል፤ አመራሮቹ ግን እርስ በርሳቸው በጉዳዩ ላይ ያላቸው አቋም የተለያየ ነው፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመድረክ ተወካይ የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ ድርድር ለመጀመር የቀረበው
Image
Such negative connotations can be sensed in segments of the southern ethnic groups, among which the  Sidama  are a major group. Kellas (1991) says that " favorable attitudes are held about the in-group and unfavorable ones about the out- ... http://books.google.com.gt/books?id=fYiPXWEg6PgC&pg=PA32&lpg=PA32&dq=sidama&source=bl&ots=oBmPlGqzna&sig=rruH5TRmPIevWnozMI5Ni1u9yns&hl=en&sa=X&ei=h6WFUMDRGYm08ATM94HwDA&ved=0CFkQ6AEwCQ

Sidama and Ethiopian: the emergence of the Mekane Yesus Church in Sidama

Image
Sidama and Ethiopian: the emergence of the Mekane Yesus Church in Sidama

How ethical is your coffee? Exploring the local stance on fair and direct trade

10.12.12   |  12:59 pm Standing in front of the coffee selection in a grocery store or a cafe is often thrilling (so much choice!), but also perplexing: Which one do I choose? Such indecision is compounded by ethical concerns due to so much coffee being sourced from the developing world. Fair Trade aims to protect coffee farmers from being exploited but criticisms of it have led to alternative models emerging like Direct Trade. Austin coffee roasters such as Third Coast Coffee, Casa Brasil and Cuvée Coffee source coffees through Fair Trade, Direct Trade or a variation of either. Each roaster aims to offer coffees that taste good and that customers can feel good about drinking, confident in the knowledge that the farmers picking the red cherry that coffee beans come from are benefiting. But true transparency for coffee traded may ultimately lie with consumers themselves. “Every time you spend money, you’re casting a vote for the kind of world you want,” said Anna Lappé, a write

EIPO to Re-Register Sidama Coffee Trademarks

Image
The Ethiopian Intellectual Property Office is finalizing preparations to conduct the re-registration of trademarks. The re-registration will be conducted on the basis of the proclamation for the registration of trademarks according to Berhanu Adelo, Director General for the EIPO. There are currently 14 thousand registered trademarks in Ethiopia with 7500 being international trademarks said Berhanu. In related news Ethiopia has managed to trademark its fine coffee brands ‘Harar’, ‘Yirgachefee’ and ‘Sidama’ internationally he noted. Efforts are also underway to trademark ‘Limu’ and ‘Nekempte’ as well as other Ethiopia’s fine coffee added Berhanu. The office is engaged in tasks to consolidate efforts to protect intellectual property rights as the number of people requesting patent rights ownership certificates is growing all the time. There were only 43 patent applications were submitted in the last financial year with the office certifying 27 patent ownership explained Be

“ኢትዮጵያ - አነቃቂ ጉዞ፤” አዲስ መጽሃፍ

Image
የኢትዮጵያን የተፈጥሮ መስህብና ቅርሶች፥ የሕዝቦቿን ባህል፤ ልማድ፥ ወጎችና አናኗር፤ እንዲሁም ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች፤ ማራኪ የመልክዓ ምድራዊ ትእይንትና ተፈጥሮ፥ በካሜራው መነጽር ቀርጾ ያስቀረውን ምስል ለአንባቢያን እይታና ንባብ ካበቃ ወጣት ባለ ሞያ ጋር የተካሄደ ቃለ ምልልስ ነው።   እሱባለው መዓዛ ይባላል። ነዋሪነቱ በዚህ በዩናይትድ ስቴትስ በአሌግዛድሪያ ከተማ ነው። ባለፉት አስር ዓመታት ውስጥ ለበርካታ ጊዜያት ወደ ልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በተደጋጋሚ ባደረጋቸው ጉብኝቶች ወቅት ባነሳቸው የፎቶ ግራፍ ምስሎች የተዋበ መጽሃፍ ነው።  “ኢትዮጵያ - አነቃቂ ጉዞ፤” ይሰኛል http://amharic.voanews.com/

የትምህርት ባለድርሻ አካላት ለተማሪ ውጤት ትኩረት እንዲሰጡ ይደረጋል

Image
ሀ ዋሳ፦ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ለተማሪ ውጤትና ሥነ ምግባር መሻሻል ትኩረት እንዲሠጡ ማድረግ የዘንድሮ የትምህርት ዘመን ቁልፍ ተግባሩ መሆኑን የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ገለጸ። በክልሉ በ2004 ዓ.ም በትምህርት ሥራ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ መምህራን፣ ርዕሳነ መምህራን፣ ተማሪዎችና ሱፐርቫይዘሮች ተሸለሙ። በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት 18ኛ አጠቃላይ የትምህርት ጉባኤ ሰሞኑን በሃዋሳ ከተማ በተካሄደበት ወቅቱ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ አህመዲን እንደገለጹት፤ የተጀመረውን የትምህርት ልማት ሠራዊት ግንባታ ሥራ በማጠናከር ባለድርሻ አካላት ለተማሪ ውጤትና ሥነምግባር መሻሻል ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ ማድረግ የበጀት ዓመቱ ቁልፍ ተግባር ነው። ባለፉት ሁለትና ሦስት ዓመታት በክልሉ በትምህርት ሠራዊት ግንባታ ሥራ መሠረት መጣሉን አስታውሰው፣ በ2005 ዓ.ም ሠራዊቱ ትክክለኛ ቁመና ተላብሶና የተቆጠረ ተግባር ወስዶ በተማሪዎች ውጤት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጣ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራ አስታውቀዋል። ዘንድሮ በትምህርት ልማት ሠራዊት ውስጥ ያሉ ባለድርሻ አካላትን ውጤት ሊያመጣ በሚችል መልኩ ለማንቀሳቀስ መታሰቡን ያመለከቱት አቶ አህመድ፤ በሚሌኒየሙና በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ የተቀመጡትን ግቦች ከማሳካት አኳያ በተያዘው ዓመት ለትምህርት ተደራሽነት ሥራም ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጥ አመልክተዋል። በጎልማሶች ትምህርት ላይም የተሻለ ሥራ ለመሥራት መታቀዱን አብራርተዋል። የትምህርትን ጥራት የሚያረጋግጥ ሥራ በዋናነት የሚመራው በመምህሩ እንደሆነ ጠቁመው፤ ክልሉ የመምህራንን አቅም ለማጎልበት የቅድመ ሥራ ላይ ሥልጠና፣ የሥራ ላይ ሥልጠናና አጫጭር ሥልጠናዎችን እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል በቅርቡ ከ35ሺ

ኢትዮጵያ የንቅናቄውን 15ኛ ዓለም ዓቀፍ ጉባዔ ከጥቅምት 12 ጀምሮ ታስተናግዳለች

Image
አዲስ አበባ ጥቅምት 10/2005 ኢትዮጵያ 15ኛውን የትብብር ለታዳጊ ከተሞችና ልማት ንቅናቄ(ኮዳቱ)ን ዓለም ዓቀፍ ጉባዔን ለማስተናገድ ዝግጅቷን ማጠናቀቋን የጉባዔው ዝግጅት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከድርጅቱ ጋር በመተባበር ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ለአራት ቀናት በአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ " የከተሞች ጉዞ ለከተሞች አደረጃጀትና እድገት" በሚል መሪ ቃል ይካሄዳል፡፡ የኮሚቴው ሰብሳቢና የአንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ በድሉ አሰፋ ዝግጅቱን አስመልክቶ ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ጉባዔው በከተማዋ የሚካሄደውን ፈጣን የለውጥ ጉዞ አጠናክሮ ለመቀጠል ያግዛል፡፡ ጉባዔው በከተማዋ በትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ዕድገት፣ ተሞክሮዎችንና አማራጮችን ለአገሪቷ በሚስማማ ሁኔታ ለመጠቀም እንደሚያስችልም አስረድተዋል። በጉባዔው ላይ ከ600 በላይ የከተሞች የትራንስፖርት አመራር አባላትና ባለሀብቶች እንደሚሳተፉበትና ከዚህ ወስጥ ከ250በላይ የሚሆኑት የአገር ውስጥ ተሳታፊዎች እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ እንዲሁም የከተማዋን እምቅ የኢንቨስትመንትና የንግድ አማራጮችን ለማስተዋወቅና የቱሪዝም መስህቦችን ለማስተዋቅ መልካም ዕድል እንደሚፈጥርም ሰብሳቢው ገልጸዋል፡፡ በጉባዔው ላይ የ30 አገሮች ተጨባጭ ተሞክሮዎች ይቀርባሉ ያሉት ሰብሳቢው፣በዚህም የሌሎች አገሮችን ልምድ ለመቅሰም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው አስረድተዋል፡፡ የጉባዔው ተሳታፊዎች አገሪቱን ለማወቅ የሚያስችላቸው ድረ ገጽ መከፈቱንና የትራንስፖርት አገልግሎት መዘጋጀቱን አቶ በድሉ ተናግረዋል፡፡ እንዲሁም በእንግሊዝኛና በፈረንሳይና ቋንቋዎች ትርጉምና መረጃ በመስጠትና በማስተላለፍ በኩል ሁለገብ አገልግሎት የሚሰጡ ወጣት ባለሙያዎች መዘጋጀታቸው