Posts

THIS UNIVERSAL DECLARATION OF HUMAN RIGHTS

Image
THIS UNIVERSAL DECLARATION OF HUMAN RIGHTS as a common standard of achievement for all peoples and all nations, to the end that every individual and every organ of society, keeping this Declaration constantly in mind, shall strive by teaching and education to promote respect for these rights and freedoms and by progressive measures, national and international, to secure their universal and effective recognition and observance, both among the peoples of Member States themselves and among the peoples of territories under their jurisdiction. Universal declaration of HR

Neoliberalism Brings Dead Ends

Image
By Meles Zenawi Meles Zenawi served as President and Prime Minister of Ethiopia between 1991 and 2012. This commentary is extracted from a draft research paper presented at Columbia University, United States, titled, Africa Development: Dead Ends and New Beginnings. The neo-liberal paradigm which suggests a non-activist and non-interventionist state, a night watchman state, as conducive to economic growth bases such conclusions on two pillars. One pillar has to do with the assertion that competitive markets are both pervasive and efficient. The second pillar has to do with a political economy based on the theory of socially wasteful rent-seeking activities and the rational choice theory of solely self-interest maximizing individuals.    Government created rent does not necessarily have to be socially wasteful.  It becomes wasteful only if solely self-interest maximizing individuals use it to create wealth at the expense of society and only if the state is incapable of imp

መለስ ዜናዊ ሲዘከሩ

Image
New የኢትዮጵያን የአምስት ሺሕም ሆነ የሦስት ሺሕ ዓመታት የመንግሥትነት ታሪክን አቆይተን ከ19ኛው ምእት ዓመት ብንነሣ፣ ጎልቶ የሚታየን ለ86 ዓመታት በመሳፍንት ተከፋፍላ ለነበረችው ኢትዮጵያ “ዘመነ መሳፍንት” ማብቃቱ በዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ መበሰሩ ነው፡፡ በተከታታይ የመጡት ነገሥታት አፄ ተክለ ጊዮርጊስ፣ አፄ ዮሐንስ፣ አፄ ምኒልክ፣ ልጅ ኢያሱ፣ ንግሥት ዘውዲቱና ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እንደየዘመናቸው ይብዛም ይነስ ተልዕኮቻቸውን ፈጽመው አልፈዋል፡፡ ተፍጻሜተ ዘውድ የሆኑትን የአፄ ኃይለ ሥላሴ ሥርዓት ለመገርሰስ የተነሣውና የፈነዳውን የየካቲት አብዮትን ተከትሎ ሥልጣኑን የተቆናጠጠው በወቅቱ ጥሪው “ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ” በኋላም ወደ ኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢሕዲሪ) በመለወጥ 17 ዓመት አገሪቱን መርቷታል፡፡ ይህ ከሆነም በኋላ ገና ሥልጣኑን በጨበጠ በመንፈቁ የትጥቅ ትግል የጀመረው የትግራይ ብሔር ድርጅት ሌሎች አጋሮቹ ከጎኑ አሰልፎ ለ17 ዓመት ያከናወነው ውጊያ በድል መጠናቀቁ ሌላኛው የታሪክ ምዕራፍ ነው፡፡ የታሪክ ፕሮፌሰሩ ባሕሩ ዘውዴ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847 እስከ 1983” ብለው ባሳተሙት መጽሐፋቸው ፍፃሜውን እንዲህ ገልጸውታል፡፡ “የኢሕዲሪ ምስረታን ያጀበው ሽብርቅና ሽርጉድ የደርግ ሥርዓት የተጠናወተውን መሠረታዊ ችግር ደብቆት ነበር፡፡ አራት ዓመትም ሳያስቆጥር፣ እንዲያ በረቀቀ ጥበብና በአያሌ ደምና ዕንባ የተገነባው ሥርዓት እንደ አሸዋ ክምር ተናደ፡፡ ደርግ ውስጥ የነበሩትን ባላንጣዎቹንና የከተሜውን ግራ ክንፍ ኃይል የሸወደው አምባገነን፣ የገጠር ሽምቅ ተዋጊዎቹን ምሕረት የለሽ የጥይት ውርጅብኝ መቋቋም አቅቶት ወደቀ፡፡ ደርግ በሰሜን ኢትዮጵያ እየተስፋፋ የመጣውን ብሔርተኛ አመፅ ለመግታት ከዐሥር ዓ

ሕዝብ ለመንግሥት የቤት ሥራ ሰጥቷል ተግባራዊ ምላሽ ይጠበቃል!

ውል ክፍል መሄድ ሳያስፈልግና ቃለ ጉባዔ መፈራረም ሳይጠይቅ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመንግሥት የቤት ሥራ ሰጥቷል፤ አደራ አቅርቧል፡፡ ተግባራዊ አዎንታዊ ምላሽም ከመንግሥት ይጠብቃል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን በሚያስገርም፣ በሚያስመካና ታሪካዊ በሆነ ሁኔታ ከልብ ገልጿል፡፡ ታሪክም ለዘለዓለም ሲዘግበው ይኖራል፡፡ በክብር መዝገብ አስፍሮታል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን ሐዘኑን ብቻ አይደለም የገለጸው፡፡ የተጀመረውን የልማት ሒደት ዳር ለማድረስም ቃል ገብቷል፡፡ አሁንም በሕገ መንግሥታችን የሰፈሩትን መብቶችና ጥቅሞች እውን ለማድረግና የኢትዮጵያን ራዕይ ዳር ለማድረስ ዝግጁነቱን ገልጿል፡፡ በእንባም፣ በቃላትም፣ በፀሎትም፣ በሠልፍም፡፡ ሕዝብ መንግሥትን ‹‹ምራ እንከተልሃለን›› ብሏል፡፡ አደራውና የቤት ሥራውም ይኼው ነው፡፡ መንግሥት ይህንን የሕዝብ አደራና የቤት ሥራ በተገቢው መንገድ በተግባር ለመመለስ መንቀሳቀስ ይጀምር፡፡ መንግሥት ይህን የሕዝብ አደራና የቤት ሥራ የሚመልሰው እንዴት ነው? ለመመለስስ ይችላል ወይ? ገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግና መንግሥት ይህን የሕዝብ አደራና የቤት ሥራ በሚገባ ከተገነዘቡትና መመለስ አለበት ብለው ካመኑበት ተገቢ ምላሽ ለመስጠት ምንም አያዳግታቸውም፡፡ ይቻላል፡፡ ለመመለስ ግን የሚከተሉትን መፈጸም አለባቸው፡፡ 1.    ቀጣይነት ሕገ መንግሥቱን መንግሥትም እንደ መንግሥት ኢሕአዴግም እንደ ገዥ ፓርቲ ያመኑበትና የተቀበሉት ብቻ ሳይሆን፣ እነሱ ሥልጣን ይዘው ባሉበት ጊዜ በራሳቸው ተነሳሽነት እውን የሆነ ነው፡፡ ስለሆነም ለቀጣይነቱ ችግር የለውም፡፡ የአምስት ዓመቱ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድም ባለው መንግሥትና ገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ የታቀደና የፀደቀ ነው፡፡ ለተግባራዊነቱ ችግር የለ

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚህ ዓለም በሞት መለየት ከተሰማ ጀምሮ መግለጫ ከሰጡት መካከል በሲዳማ ዞን ስር የሚገኙ የንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ፣ መንገዶችና ትራንስፖርት መምሪያ፣ የዳሌ ወረዳ አስተዳደር በሃዋሳ ከተማ የዳካ ቀበሌ ታዳጊ ተማሪዎች ህብረት፣ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ እንዲሁም የሀዲያ ዞን ንግድና ኢንዲስትሪ ልማት መምሪያ ይገኙበታል፡፡

ባለራዕይና የዘመናችን ታላቁ መሪ መለስ ዜናዊ ሁሉአቀፍ እውቀትና የመምራት ብቃት ያላቸው በሳል መሪ ነበሩ ብለዋል፡፡ በተመሳሳይም በይርጋዓለም ከተማ የሠላም አንድነት አረጋዊያን ማህበር የተስፋ ራዕይ አውራጅና ጫኝ ማህበር፣ ራይስ ኢንጀነሪንግ ኒያላ ሞተርስ፣ ሲዳማ ቡና አቅራቢዎች ማህበር፣ ፖራዳይስ ሆቴል፣ ይርጋዓለም ኮንስትራክሽንና  ኦሲስ ሆቴል ውስጥ የሚገኙ ሠራተኞች፣ ሃላፊዎቹና ባለቤቶቹ የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል፡፡ መሪያችን የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ አሌኝታ  የሆኑ ታላቅ ሰው ነበሩ ያሉት መግለጫ  ሰጪዎቹ በእሳቸው የተጀመሩትን እቅዶች ተግባራዊ በማድረግ ስራቸውን ከመቃብር በላይ ሲታወሱ እንዲኖሩ እናደርጋለን ብለዋል፡፡ በተለይም ይህን የሰነቁትን ዓላማ ወጣቱ ትውልድ በደንብ ተገንዝቦት በጋራ የመረባረቡን ሃላፊነት እንዲወጣ አደራቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብና ቤተሰቦቻቸውን መፅናናትን እንመኛለን ብለዋል፡፡

የሲዳማ ዞን ነዋሪዎች መንግስት በዞኑ የምፈጸመውን የሰብኣዊ መብት ረገጣ፡ እስር እና እንግልት እንዲያቆም ጠየቁ፤ በመንግስት ላይ ህዝብን በማነሳሳት በምል የታሰሩ ግለሰቦች ያለ ምንም ቅድሜ ሁኔታ እንዲፈቱ ኣሳሰቡ።

የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ሪፖርተሮች ተዘዋውረው ያኗገራቸው የዞኑ ነዋሪዎች እንደተናገሩት፤ መንግስት በሰበብ ኣስባቡ የተለየ ኣመለካከት እና ኣስተሳሰብ የምያራምድ ግለሰቦችን በኣስፈለገው ጊዜ እና ወቅት የተለያዩ ስሞችን በመስጠት በማስር ላይ ነው። በሃዋሳ ከተማ ሌዊ ሆቴል ሲዝናኑ ያገኘናቸው ካላ ጌታሁን ሳርምሶ የተባሉ በከተማዋ የኣዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ነዋሪ እንደተናገሩት፤ መንግስት በተለያዩ ጊዚያት በተለይ ከክልሉ ባለስልጣናት ፖለቲካዊ ኣመለካት የተለየ ያለ ኣመለካከት ያላቸውን ግለሰቦች ማሰሩ የተለመደ ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰው በኣሁኑ ጊዜ በተለይ ከሲዳማ የፊቼ በዓል ማግስት ጀምሮ በርካታ ሰዎች ህዝብን በመንግስት ላይ በማነሳሳት ተከሰው ታስረዋል። ግለሰቦች የመሰላቸውን ፖለቲካዊ ሆነ ማህባራዊ ኣመለካከትን ያለ ምንም ገደብ እንዲያራምዱ በምፈቅድ ህገ መንግስት ባለባት ኣገር ግለሰቦች የተለየ ኣመለካከት ስላላቸው ብቻ ስብኣዊ መብታቸው መጣሱ ኣግባብነት የለውም ብለዋል። ወጣት ንቆዲሞስ ኣየለ የተባለ በሃዋሳ ከተማ የባጃጂ ታክሲ ሽፌር በበኩሉ፤ የሲዳማ ክልል ይገባኛል ጥያቄ በተመለከተ ህዝባዊ ንቅናቄ  ከተጀመረ ወዲህ በተለይ ወጣቶች  በመንግስት የጸጥታ ሰዎች ማስፈራሪያ እንደምደርሳቸው ገልጿ፤ ለህዝቡ ጥያቄ ኣግባብነት ያለውን ምላሽ መስጠት እንጂ ሰዎችን ማስር እና ማንገላት መፍትሄ ኣይደለም ብለዋል። ካላ ዘርሁን ናራሞ የተባሉ በተለምዶ ስሙ ሊዝ ሰፈር በምባለው ኣከባቢ መንገድ ላይ ሲጓዙ ያገኘናቸው የሃዋሳ ከተማ ነዋሪ፤ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሃዋሳ ከተማ ብሎም በሲዳማ ዞን ወረዳዎች ውስጥ ግለሰቦች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ከመኖሪያ ቦታቸው እና ከስራ ገበታቸው እየተያዙ እንደምታሰሩ ጠቅሰው፤ ግለሰቦች በተጠረጠሩት ጉዳይ ላይ

የቡና ዋጋ ቅናሽ ማሳየት እያነጋገረ ነው

Image
ቃልዲ በኢትዮጵያ ምድር የገዘፈ ታሪክ ባለቤት ነው፡፡ በዘጠነኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ ይሆናል። ከከፋ መንደር ፍየሎች ጥዑም ፍሬን አገኙ። የመንጋው እረኛ ብላቴናው ቃልዲ ከዛን ዘመን ጀምሮ ስሙ በታሪክ ማኅደር ሰፈረ። ምክንያት የሚያግዳቸው ፍየሎች ለሀገሬውና ለዓለም ሕዝብ ቡናን በማሳወቃቸው ነው። ምስጋና ለእነርሱ ይሁንና ይኸው ዛሬም ድረስ ኢትዮጵያ ከጥዑም ቡናዋ እረኛው ቃልዲም ከታላቅ ስሙ ጋር ተቆራኝተው ለዘመናት መዝለቅ ችለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ካሉ ሰባት ታዋቂ ቡና አምራች ሀገራት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉርም በዘርፉ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳለች። በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ውስጥ ሰፊ ድርሻ ያለው ቡና ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ ፋይዳ የጀርባ አጥንት ነው። ከሌሎች የግብርና ምርቶች ቡና ከአገር ውስጥ ተጠቃሚዎች አልፎ ለበርካታ ሀገራት በመቅረብም የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት ረገድ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ያለተቀናቃኝ በአውራነት ሊዘልቅ ችሏል። ኢትዮጵያ ቡናን ለመጀመሪያ ጊዜ ለባህር ማዶ ገበያ ያቀረበችው በፈረንጆቹ የዘመን አቆጣጠር 1838 በምጽዋ ወደብ በኩል እንደነበር ታሪክ ይነግረናል። በ19ኛው ክፍለ ዘመን ሁለት የቡና ዓይነቶችን ( ሐረር እና አቢሲኒያ) ለንደንን ጨምሮ ወደ ኒውዮርክ እና ማርሴል ከተሞች በመላክ የኤክስፖርት ንግዱን ተያያዘችው። ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የኤክስፖርት ግብይት በአሁኑ ወቅትም በጥራት እና ብዛት ዕድገት እያሳየ ዘልቋል። ሆኖም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በግብይት ሥርዓቱ ውስጥ የሚፈጠሩ የተለያዩ መሰናክሎች ሳቢያ አርሶ አደሮች የጥረታቸውን ያህል ተጠቃሚ ነበሩ ለማለት ያዳግታል። ከፍተኛ የቡና ምርት መገኛ እንደሆኑ በሚነገርላቸው የተለያዩ አካባቢዎች የኅብረት ሥራ ማኅበራት መመሥረትን ተከት

የኢትዮጵያን የውክልና ሕግ ቢያውቁ ይጠቀማሉ

በኤልያስ ዶጊሶ  ከደቡብ ክልል ፍትህ ቢሮ  እጅግ እየዘመነ በመጣው የዓለማችን የኑሮ ሁኔታ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሕልውና ጥያቄ ሆኗል። በተለይ ሕዝቦች ከከፋ ድህነት ተላቅቀው የተሻለ ሕይወት መምራት እንዲችሉ በኢኮኖሚው መስክ ንቁ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ይጠበቃል፡፡ እንደ ንግድ ያሉ የኢኮኖሚ ዘርፎች ደግሞ አንዳንዴ በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት የተለያየ ስፍራ መገኘትን ይጠይቃል። የሰው ልጅ ደግሞ በተፈጥሮው በጊዜና በቦታ ውሱን ከመሆኑ አንፃር በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት ጥቅሙን በሚመለከቱ ስፍራዎች ሁሉ ተገኝቶ ተግባሩን መከወን አይችልም፡፡ እነዚህ መሰል ጉዳዮችን አስመልክቶ የሰው ልጅ የሚኖረው ብቸኛ አማራጭ እንደራሱ ሆኖ በእርሱ እግር ተተክቶ ጉዳዮቹን ወይም ሥራዎቹን የሚከውንለትን ሰው መወከል ግድ ይሆንበታል፡፡ ሥራዎችን በውክልና ማሰራት አስፈላጊ የሆነው በኢኮኖሚው ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በማህበራዊ የሕይወት መስክም ካለው ጠቀሜታ አኳያ ነው፡፡ በየትኛውም ዘርፍ የሚደረጉ የውክልና ውሎች ማዕቀፋቸው በፍትሐብሔር ሕግ ከአንቀጽ 2179 እስከ 2285 ባሉ ድንጋጌዎች ነው፡፡ በዚሁ ሕግ መሠረት የውክልና ሕግ የእንደራሴነት ሕግ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ሁለቱንም ቃላት መጠቀም በፍቺ ረገድ ልዩነት የላቸውም፡፡ በአማርኛ መዝገበ ቃላት «ወኪል» የሚለውን ቃል እንደዋና ሆኖ የሚሰራ፣ ተጠሪ፣ ኃላፊ፣ ዋናውን ተክቶ እንዲሰራ የተመረጠው ሰው፣ አካል የሚል ሲሆን «ውክልና» ማለትን ደግሞ ለአንድ ሰው ወይም ድርጅት ወኪል፣ ተጠሪ መሆን የሚል ፍቺ ተሰጥቶታል፡፡ በፍ/ሕ/ቁ 2199 መሠረት ደግሞ «ውክልና» ማለትን በሚከተለው መልኩ ይተረጉመዋል፡፡ «ተወካይ የተባለ አንድ ሰው ወካይ ለተባለው ሰው እንደራሴ ሆኖ አንድ ወይም ብዙ ሕጋዊ ሰራዎችን በወካዩ ስም ለማከናወን ግዴታ የሚገባበት ውል ነው።

ኣስቂኝ ዜና ስለ ኣቶ መለስ እና የፕሬስ ነጻነት

Image
በተለይ በላፉት ኣምስት ኣመታት የሚዲያ ነጻነት ኣፊነው ጋዜጤኞችን በየጊዜው በሰበብ ኣስባቡ ከከርቼሌ ዘብጥያ ስወረውሩ የቆዩትን መሪ ለሚዲያ ነጻነት ታግለዋል ብሎ የሚያወድስ ዜና መስማት ኣያስቂም? ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የፕሬስ ነፃነት እንዲከበር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል  -የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን አዲስ አበባ፡- የኢትዮጵያ ብሮድ ካስት ባለስልጣን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በኢትዮጵያ የፕሬስ ነፃነት እንዲከበር ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ መሪ እንደነበሩ ገለጸ። ባለሥልጣኑ ለዝግጅት ክፍላችን በላከው መግለጫ የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት ጥልቅ ኀዘን እንደተሰማቸው ገልጿል።  ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቤተሰቦችና ለኢትዮጵያ ህዝብም መጽናናትን ተመኝቷል።  ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዜጎች ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ህገ መንግሥታዊ ዋስትና አግኝተው ተግባራዊ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል። በኢትዮጵያ የፕሬስ ነፃነት እንዲከበር ማድረግ የአመለካከት እና ሀሳብን በነፃ የመያዝና የመግለጽ መብት እውን እንዲሆን ሰርተዋል ብሏል። አገሪቱ ከኋላ ቀርነት እና ከድህነት ተላቅቃ በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስሟ በመልካም እንዲጠራ የሰሩ እሩቅ አሳቢና ባለዕራይ ነበሩ። ያለው የባለሥልጣኑ መግለጫ፣ እሳቸው የጀመሩትን የሰላም የልማትና የዴሞክራሲ መስመር በመከተል ለማሳካት ጠንክሮ እንደሚሰራ አረጋግጧል። http://www.ethpress.gov.et/ethpress/main/news.php?newsLocation=home&newsInstruction=headline&newsId=9252

Food Production and Food Losses

People in all over the world produce their foods in their own peculiar way and system of production. The way an American farmer grows food compared with their Ethiopian counterparts are beyond comparison. The number of people who are engaged in agriculture in America is said to be only three percent of the total population while 87pct of the Ethiopian population are agriculturalists. However, the American farmers are net food exporters contrary to the large majority Ethiopians who are subsistence farmers and food insecure. This is not God’s curse against the Ethiopians; rather it is the huge difference in their level of development and production systems.  As in their food production, there is also marked difference between America and Ethiopia in the amount of their food losses. The amount of food losses in America is so large that it is incomparable with the food Ethiopia loses which is very minimal. The same is true with America and other developing countries. The same reality is a

Hawassa University Expresses its grief on the death of our late Prime Minister His Excellency Mr. Meles Zenawi. The University wishes strength for his family and the Ethiopian People.

Image
продвижение сайтов Hawassa University Expresses its grief on the death of our late Prime Minister His Excellency Mr. Meles Zenawi. The University wishes strength for his family and the Ethiopian People.

በኢትዮጵያ ህይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን የደቡብ ኢትዮጵያ ህብረት ጽህፈት ቤት ፣ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሀዋሪያት ቤተክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት፣ የሀዋሣ ጐተራ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን ጽህፈት ቤት በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለፁ፡፡

  በኢትዮጵያ ህይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን የደቡብ ኢትዮጵያ ህብረት ጽህፈት ቤት ፣ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሀዋሪያት ቤተክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት፣ የሀዋሣ ጐተራ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን ጽህፈት ቤት በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለፁ፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒሰትሩ የሀገራችን የልማት ሀዋሪያ፣ የምን ጊዜም ጀግና ፣ የፍሪካ ኩራት ናቸው፡፡ በሞት ቢለዩንም ህያው ሥራዎቻቸው በኢትዮጵያውያን ልብ ሲታወሱ ይኖራሉ ብለዋል፡፡   ለሀይማኖት መስፋፋት፣ ነፃነትና እኩልነት የተጉ መሪ እንደነበሩ ያመለከቱት መግለጫ ሰጪዎች በክልሉ የሚገኙ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች እጅ ለእጅ ተያይዘን የተጀመሩ የልማት ተግባራትን ከዳር ለማድረስ ቆርጠን እንሠራለን ብለዋል፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/21NehTextN604.html  

የሲዳማ ዞን ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መመሪያ፣ የእዥ ወረደ አስተዳደር በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸውን ሐዘን ገልፀዋል፡፡

ክቡር ጠቀላይ ሚኒስትር የሴቶችንና የወጣቶችን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን እንዲሁም የህፃናትን መብትና ደህንነት ለማስጠበቅ ምቹ የሆኑ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በመንደፍና ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል፡፡ በርሳቸው አመራር ኃላ ቀርነትን ታሪክ ለማድረግና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል መሠረት ተጥሏል፡፡ ይሁን እንጂ ባጋጠማቸው ድንገተኛ ሞት የከፋ ሀዘን ተሰምቶናል ብለዋል፡፡   በተመሳሳይ የሀዋሳ እርሻ ልማት ድርጅትና የኢትዮጵያ መፅሐፍ ቅዱስ ማህበር ሀዋሣ ቅርንጫፍ ሀገራችንን በበሳል አመራር ላለፉት 21 አመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በመምራትና ትክክለኛ የእድገት መንገድ በመቀየስ መሪ ሚና የተጫወቱት ክቡር ጠቅላይ ሚኒሰትር በመለየታቸው ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማቸው አመልክተዋል፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/21NehTextN204.html

የሲዳማ ሕዝብ የሀገር ኩራት በሆነው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማውን መሪር ሀዘን ሲገልጽ ለመላዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲሁም ለቤተዘመዶቹ መጽናናትን በመመኘት ነዉ !! ይሁንና በርካታ የሲዳማ ብሔር ተወላጆች በማይታወቅ ምክንያት ታስረዉ ይሄን ብሔራዊ ሀዘን ለመካፈል ባለመቻላቸዉና የዋስ መብት እንኳን በመነፈጋቸዉ እሮሮአቸዉን በማሰማት ላይ ይገኛሉ፡፡ (ከማህበራዊ መረብ ላይ የተገኘ ጽሁፍ)

Image
የሲዳማ ሕዝብ የሀገር ኩራት በሆነው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማውን መሪር ሀዘን ሲገልጽ ለመላዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲሁም ለቤተዘመዶቹ መጽናናትን በመመኘት ነዉ !! ይሁንና በርካታ የሲዳማ ብሔር ተወላጆች በማይታወቅ ምክንያት ታስረዉ ይሄን ብሔራዊ ሀዘን ለመካፈል ባለመቻላቸዉና የዋስ መብት እንኳ በመነፈጋቸዉ እሮሮአቸዉን በማሰማት ላይ ይገኛሉ፡፡  በሕገ-መንግስቱ በአንቀጸ 39 ላይ የተደነገገውን መብት እስክንጎናጸፍ ድረስ የማንነት ጥያቄአችን ከምንም ጊዜ በላይ ተጠናክሮ ይቀጥላል፤ በምንም ዓይነት ሁኔታ አይቆምም!!! ውድ የሲዳማ ብሄር ተወላጆች በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የምትገኙ በሙሉ እንኳን በዓይነቱ ልዩ ለሆነውና በሲዳማ ታሪክ የመጀመሪያ ሊባል ለሚገባው ለ2005 ዓ.ም ሲዳማ የዘመን መለወጫ fichee cambalaalla በዓል ለማየት፣ለመስማት አበቃችሁ/ በሰላም አደረሳችሁ/ን/!!  የሲዳማ ዘመን መለወጫ የfichee cambalaalla በዓል ነሐሴ 9/2004/ በሲዳማ ቀን አቆጣጠር መስከረም 1/ 2005 ዓ.ም በአስገራሚ ሁኔታ ከዚህ ቀደም በታሪክ ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ መልኩ በዓሉን ለማክበር ከየአቅጣጫዉ ወደ ሀዋሳ የመጡት የብሔሩ ተወላጆች ብቻ ሌሎች ታዳሚዎችን ሳይጨምር በጥቂቱ ቁጥራቸው ወደ 2.5ሚሊየን የሚጠጉ በባህላዊ አጋጌጥ ተውበው ጦርና ጋሻቸውን አንግበው በዋና ከተማቸው በድምቀት ለማክበር በቄጣላ በመግባታቸው የከተማውን ሕዝብ ጉድ ያስባለና ያስደነቀ ታሪካዊ በዓል መሆኑ ይታወሳል፡፡  በዕለቱም ሰፊው የሲዳማ ሕዝብና የበዓሉ ታዳሚዎች/ተጋባዥ እንግዶች በዓሉን እንደጓጉለት ለማክበር አልታደሉም፡፡ በዓሉን ለማክበር የወጣውን የሕዝብ ብዛት ከሩቁ የተመለከቱና ከየአቅጣጫው በቄጣላ የዘመኑ የሙዚቃ ቅንብር በማይተካ መ