Posts

ከተለያዩ የሲዳማ ዞን ወረዳዎች የተወጣጡ ሰዎች ለኣቶ መለሰ ዜናዊ በሲዳማ ባህል መሰረት እንጨት ተክሎ ማልቀሳቸው ተሰማ

በትናንትናው እለት ቁጥራቸው ከሶስት ሺ በላይ የሚሆኑ የሲዳማ ዞን ነዋሪዎች በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት ለኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኣቶ መለስ ዜናዊ በሃዋሳ ከተማ በሲዳማ ባህል መሰረት ኣልቅሰዋል። በሲዳማ ባህል መሰረት ለጀግና እንደምለቀሰው ሁሉ ለኣቶ መለሰ ዜናዊም እንጨት ተተክሎ ቀይ ተቀብቶ የተለቀሰላቸው ሲሆን፤  'ጎባ ባኢታ ኣና ሆጌ' እያለ በቄጣላ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት የተሰማውን ሀዘን ገልጿል። በሃዘን መግለጫ ስነስርዓቱ ላይ ከሽማግሌዎች የተወከሉ እና የክልል መንግስቱ ባለስልጣናት ንግግር ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸው በኣቶ መለሰ ዜናዊ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ከዳር እንዲደርሱ ሁሉም በጋራ እንዲሰራ ጥር ኣቅርበዋል። በስነስርዓቱ ላይ የክልል እና የሲዳማ ዞን ባላስልጣናትን ጨምሮ የሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች እና መንግስት ባዘጋጃቸው መኪኖች ባህላዊ ልብስ እንዲለብሱ ተደርገው ከየወረዳዎቹ የተጋበዙ ሰዎች መገኘታቸውን ወራንቻ ኢፎርሜሽን ኔትዎርክ ዘግቧል ።  

Ethiopia: Power scramble after premier’s death puts fragile state on the edge

Image
By Juma Kwayera Who is the Prime Minister? Aug 26, 2012, Nairobi (Standard) — Governing Ethiopia People’s Revolutionary and Democratic Front (EPRDF) faces an uncertain future following the death of Prime Minister Meles Zenawi. Ethnicity, as ever, is going to determine who takes over the reins of power. A week after Zenawi’s death was made public, the scramble for power has intensified with the members of the politburo of EPRDF said to be slugging it out, pointing to an imminent political turbulence or even a falling out. At the centre of the ensuing power struggle is acting Prime Minister Hailemariam Desalegn, his predecessor at the Foreign ministry and ambassador to China Seyoum Mesfin and Zenawi’s widow Azeb Mesfin, who had been tearing into each other long before the fallen Prime Minister became indisposed. There are also prominent political figures in the governing party Zenawi had suppressed as he maintained a stronghold on power. Smooth transition Altho

የሳምንቱ ምርጥ ጎል በገብረ ስላሴ

Image
New

ዩ ኤስ ኤ ኣትላንታ የሚኖሩ የሲዳማ ዲያስፖራ ኮሚኒት ኣባላት በሲዳማ ዞን የክልል ጥያቄን ኣስመልክቶ የተቀጣጠለው ህዝባዊ ንቅናቄ ተጠናክሮ መቀጠል ኣለበት ኣሉ፤ የሲዳማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክልል ጥያቄውን የመምራት ኃላፊነት እንዲዎስዱ ጠየቁ

Image
New ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ በኣሜሪካን ኣገር በኣትላንታ ነዋሪ የሆኑ ኣንዳንድ የሲዳማ ዳይስፖራ ኮሚኒት ኣባላት ለወራንቻ ኢፎርሜሽን ኔትዎርክ እንደተናገሩት፤ ከሁለት ወራት ጀምሮ  በመላዋ ሲዳማ የተቀጣጠለው የክልል ጥያቄ ማዕበል ተጠናክሮ መቀጠል ኣለበት። መንግስት የሃዋሳን ከተማ ኣስተዳደር ከሲዳማ እጅ ለመንጠቅ ያደረገው ጥረት መክሸፉን ተከትሎ ጊዜ እየጠበቀ የሚነሳው የሃዋሳን ከተማ ኣስተዳደር በጋር ማስተዳደር የሚል የክልል መንግሥት ኣመለካከት ያንገሸገሻቸው የሃዋሳ ከተማ ባለቤቶች ያነሱት የክልል ይገባኛል ጥያቄ ያለ ምንም ቅድሜ ሁኔታ መቀጠል ኣለበት ያሉት ዳያስፖራዎቹ፤ ኣዲሱ የኢትዮጵያ መንግስት ኣመራር ሀገ መንግስቱን መሰረት ባደረገ መልኩ ለህዝባዊው ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ መስጠት ኣለባቸው ብለዋል። የሲዳማ ህዝብ ክልል ይገባኛል ጥያቄ  ሲያነሳ ለመጀመሪያ ጊዜ ኣለመሆኑን ያስታወሱት እነኝው ኣስተያየት ሰጪዎች፤ የዛሬ ኣስር ኣመት በተመሳሳይ መልኩ የተነሳው የህዝባዊ ጥያቄ በዞኑ ምክር ቤት ኣባላት ጭምር ተቀባይነት ኣግኝቶ መቶ በመቶ ድጋፊ ለሚመለከተው ኣካል መቅረቡ ተናግረዋል። ይሁን እና በጊዜው የሚመለከተው የመንግስት ኣካል የክልል ይገኛል ጥያቄውን በልማት እንዲቀየር ባቀረበው ኣማራጭ የክልል ጥያቄ ተደብስብሶ የታለፈ ቢሆንም በሰፊው የሲዳማ ህዝብ ልብ ውስጥ ግን ተቀብሮ  መቅረቱ ኣሁን ለሁለተኛ ጊዜ ጥያቄውን እንዲያነሳ ማገደዱን ኣስረድዋል። በኣሁኑ ጊዜ ለሁለተኛ ጊዜ የተነሳው ክልል ይገባኛል ጥያቄ እንደከዚህ በፊት በተለያዩ ማባቢያዎች ተደብስብሶ  እንዳይቀረ ህዝቡ በመንግስት ማባቢያዎች ሳይታለል ለጥያቄ መሳከት ተግተው እንዲሰራ ኣደራ ብለዋል።  ኣክለውም የህዝቡን ጥያቄ  ለሚመለከተው መንግስታዊ ኣካል ለማቅረብ በሽማግሌ

የሲዳማ ዞን ግብርና መምሪያ አመራሮችና ሠራተኞችን ጨምሮ በደቡብ ክልል የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና ማህበራት በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸወን ሀዘን እየገለጹ ነው

በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት መሪር ሀዘናቸዉን የገለጡት የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ልማት ማህበርና ፣በጋሞ ጎፋ ዞን የጨንቻ ወረዳ አመራሮች፣ ሠራተኞችና ወጣቶች፣ የክልሉ መምህራን ማህበር ጽህፈት ቤት አመራርና ሰራተኞች ፣የቡታጅራ ፍሬ ደረጃ አንድና ሁለት፣ደቡብ አድማስ ደረጃ ሶስት መለስተኛና አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ባለንብረቶች ማህበር ናቸዉ ። በተጨማሪ የሲዳማ ዞን ግብርና መምሪያ አመራሮችና ሠራተኞች ፣የደቡብ ኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ሞት የተሰማቸዉን ጥልቅ ሀዘን ገልጠዋል ። ተቋማቱና ማህበራቱ ባስተላለፉት የሀዘን መግለጫ የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ድንገተኛ ሞት መሪር ሀዘን ያሳደረብን ቢሆንም እርሳቸው ጥለውልን ያለፏቸውን መልካም ስራዎች፣ ፖሊስዎችና ስትራቴጂዎችን በማስቀጠል ራእያቸዉን እናሳካልን ሲሉ በአንድ መንፈስ አረጋገጠዋል ። ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከአባይ ወንዝ አገራችን ተጠቃሚ እንድትሆን እስከ ዛሬ የነበሩ የትኛዎቹም የኢትዮጵያ መንግስታት ያለደፈሩትን የታላቁን የሀዳሴ ግድብ ግንባታ በማስጀመር ጀግንነታቸዉን በገሀድ ያሳዩና መላዉን ኢትዮጵያዊ ያኮሩ መሪ መሆናቸዉን በመግለጫቸዉ አስታዉቀዋል ። በብልሁ መሪያቸን የተጀመሩ የልማት ስራዎችን እንዲሁም የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅዱን ለማሳካት ከመቼውም በበለጠ ጠንክረን እንስራለን ሲሉ በቁጭት አረጋግጠዋል ።

7 አባላትን ያቀፈ አንድ ቡድን ሀገሪቱን የመምራት ስራ ተረከበ

Image
ኢሳት የዲፕሎማቲክ ምንጮቹን ጠቅሶ ትናንት እንደዘገበዉ የቀድሞዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአሁኑ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር በሆኑት በአቶ ስዩም መስፍን የበላይነት የሚመራ 7 አባላትን ያቀፈ አንድ ቡድን ሀገሪቱን የመምራት ስራ የተረከበ ሲሆን ፤ 4 አባላቱ የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣናት ናቸዉ፡፡  ምንም እንኳን ሐይለማሪያም ደሳለኝ በግዜያዊነት ጠቅላይ ሚኒስትሩን በመተካት የአመራሩን ቦታ እንደተረከቡ በኢትዮጵያ መንግስት በይፋ ቢገለፅም ሀገሪቱን የመምራት ስልጣን ግን በዚህ ቡድን እጅ ነዉ ሲል ያተተዉ ይህ የኢሳት ዘገባ ቡድኑ የትግራዮች የበላይነት በሰፊዉ የነገሰበት ነዉ ሲል አብራርቷል፡፡ በዚህ የኢሳት ዘገባ እንደተገለፀዉ በአቶ ስዮም መስፍን በሚመራዉ ቡድን ዉስጥ ምክትል የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት አቶ ብርሀነ ገብረ ክርስቶስ በምክትል ሊቀመንበርነት የተሰየሙ ሲሆን ፤ የመከላከያ ኢታማጆር ሹም የሆነዉ ጀኔራል ሳሞራ የኑስና የሀገሪቱ የፀጥታ መስሪያ ቤት ሀላፊ አቶ ጌታቸዉ አሰፋ በአባልነት ይገኙበታል፡፡ ተያይዞም እንደተጠቆመዉ በቡድኑ ዉስጥ ከብአዴን ፣ ኦህዴድና ዴህዴን አንድ አንድ አባላት ተካተዋል፡፡ ቡድኑ ላዕላይና ታህታይ በሚል መዋቅር የተከፈለ ነዉ ያለዉ የኢሳት ዘገባ ምንም እንኳን በላዕላይ የአመራር መዋቅር ዉስጥ አጋር ድርጅቶች ባይሳተፉም በታችኛዉ መዋቅር ዉስጥ ይገኛሉ ሲል ጠቁሟል፡፡ ዘገባዉ አያይዞ እንደገለፀዉ ስርዓቱ ይህንን የአመራር ቡድን ለመፍጠር የተገደደዉ ምራባዉያኑንም ያስማማዉ በህወሓት ዉስጥ ጭምር በታየዉ የጎላ መከፋፈል ምክንያት ሁሉን የሚያስማማ መሪ መምረጥ አስቸጋሪ ሁኖ በመገኘቱ ነዉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ከታሰቡ ሰዎች መካከል አቶ ስዩም መስፍንን ጨምሮ ዋና ዋና የህወሓት ባለስልጣናት የፓርላማ አባል

የሲዳማ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ ዓለም ኣቀፍ ዘመቻ እየተካሄደ ነው

ከሲዳማ ክልል ጥያቄ ጋር ተያይዞ ህዝብ በመንግስት ላይ በማነሳሳት ወንጀል ተከሰው በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች የታሰሩ የሲዳማ ተወላጆች እንዲፈቱ ዓለም ኣቀፍ ዘመቻ እየተካሄደ ነው። የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቀው ፕቲሽን በተለያዩ ማህበራዊ መረቦች በሰራጨት ላይ ሲሆን፤ በርካታ ሲዳማ ተወላጆች እና ተሰብኣዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች እና ግለሰቦች በመፈረም ላይ መሆናቸው ታውቋል። እስረኞቹ እንዲፈቱ የምጠይቀውን ፕቲሽን ለመፈረም እዚህ ላይ ይጫኑ፦ Free Sidama Prisoners

One woman working to lift nine others out of poverty with her

Image
 Photo: Josh Estey/CARE tags:  CARE Australia ,  CARE ,  Africa ,  Ethiopia ,  Women's empowerment ,  Food insecurity ,  village savings and loan ,  WE-RISE , Bare for the basics By Kevin Hawkins, Development Education intern Help raise awareness for women like Sherbato who go without the basics everyday – visit   Go Bare to give women the basics . Looking after a large family can be tough. Looking after a large family alone is even tougher, especially if you are a single woman, living in poverty in a rural Ethiopian village. In Ethiopia, families have almost six children on average , and caring for a large family can put a lot of stress on many parents. This is particularly true in the Sidama Zone, where food insecurity is high and weather unreliable. Sherbato Adamo’s family has even greater challenges, as she has been taking care of her children alone after her husband died twelve years ago. Sherbato Adamo’s husband died 12 years ago, leaving

Requiem for a Reprobate: Ethiopian Tyrant Should Not Be Lionized

Image
Thor Halvorssen , Contributor OP/ED   |   8/22/2012 @ 4:16PM  | 19,549 views Requiem for a Reprobate: Ethiopian Tyrant Should Not Be Lionized By  Thor Halvorssen  and Alex Gladstein With the dust beginning to settle on yesterday’s death of Meles Zenawi—ruler of Ethiopia since 1991—Western leaders have been quick to lavish praise on his legacy. A darling of the national security and international development industries, Zenawi was  applauded  for cooperating with the U.S. government on counter-terrorism and for spurring economic growth in Ethiopia—an impoverished, land-locked African nation of 85 million people. In truth, democratic leaders who praise Zenawi do a huge injustice to the struggle for human rights and individual dignity in Ethiopia. Meles Zenawi at the World Economic Forum summit in Addis Ababa in May 2012 (Photo: WEF) U.S. Ambassador Susan Rice said Zenawi “ leaves behind an indelible legacy of major contributions to Ethiopia, Africa, and

SLF Statement on the Death of Meles Zenawi

August 22 2012-The 21 years of Meles Zenawi’s rule were continuation of brutalization and suffering of Sidamas people that have even worsened during his iron-fisted rule.  Now, Meles is gone, but the system he championed has continued preying on Sidama innocents. Even, as he was fighting for his life at undisclosed location, hundreds of Sidamas were unlawfully arrested and thrown into jails. The army that was deployed throughout the Sidama has continued intimidation and terrorizing Sidama people. The former president of South Nation Nationalities and People Regional Government and possible successor of Meles Zenawi, Hailemariam Desalegn, is the main architect of Loqqe massacre, one of worst atrocities ever committed on sidama soil. He is also behind ill-devised policies that targeted Sidama for past 10 years.  The demise of Meles Zenawi may open window of opportunity to end the suffering of people in Ethiopia if the ruling party were to stop pursuing the same failed policy of past tha

የኣቶ መለስ ዜናዊን ሞት ተከትሎ በሲዳማ ሲጧጧፍ የነበረው እስር ጋብ ማለቱ ተገለጸ

የሲዳማ ክልል ጥያቄን ኣንግቦ በተቀጣጠለው ህዝባዊ ንቅናቄ ህዝብን በመንግስት ላይ በማነሳሳት በምል ሃዋሳ ከተማን ጭምሮ በተለያዩ የሲዳማ ወረዳዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ይካሄድ የነበረው ግለሰቦችን የማሰር እንቅስቃሴ ጋብ ብሏል። በኣለፉት ሶስት ሳምንታት ውስጥ ከሃምሳ በላይ የሚሆኑ ግለሰቦች መታሰራቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ከታሰሩት ማካከል ካላ ብርሃኑ ሀንካራን ጨምሮ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ሃዋሳ ከተማ ከምገኘው ፍርድ ቤት የቀረቡ ወደ ኣስር የሚሆኑ ግለሰቦች ቀጠሮ ተሰጥቷቸው ወደ ማረሚያ ቤት ተመልሰዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኣቶ መለስ ዜናዊን ይተካሉ ተብሎ የሚጠበቁት የኣገሪቱ ምክትም ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኣቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በሲዳማ የክልል ጥያቄን በተመለከተ በምኖራቸው ኣቋም ላይ የተለያዩ ኣስተያዬቶች እየተሰጡ ነው። ያነጋገርናቸው  ካላ ደመቀ ዳንጋሞ እና ቤላሞ ባሻ   የሃዋሣ ከተማ ነዋሪዎች እንደምሉት ከሆነ፤ ኣቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከሲዳማ ህዝብ ጋር የኖሩና ሲዳማን ህዝብ ጠንቅቀው የሚያውቁ በመሆናቸው ለክልል ጥያቄው ኣዎንታዊ ምላሽ ልሰጡ ይችላሉ። ይህንን ኣስተያየት የተቃረኑት ካላ ኣስፋ ላላንጎ እና ካላ ናኦራ ቡኤ በበኩላቸው፤ ኣቶ ኃይለማርያም ካለፉት ኣስር ዓመታት ጀምሮ ጸረ ሲዳማ ኣቋም ያላቸው እና ከኣስር ኣመታት በፊት በርካታ ሲዳማዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እንዲገደሉ ካደረጉት የደቡብ ክልል ባላስልጣናት መካከል ኣንዱ በመሆናቸው የክልል ጥያቄውን በተመለከት የሚኖራቸው ኣቋም ኣዎንታዊ ልሆን ኣይችልም ብለዋል። ክቡራን የብሎጋችን ኣንባቢያን የሲዳማ ክልል ጥያቄ እና የወደፊት እጣ ፋንታ በተመለከተ ያላችሁን ኣስተያየት በሚከተለው ኣድራሻ ላኩልን፦ no

Life after Ethiopia's Meles Zenawi - Inside Story - Al Jazeera English

Life after Ethiopia's Meles Zenawi - Inside Story - Al Jazeera English New

ኢትዮጵያ ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ በኋላ

Image
በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት ምክንያት በኢትዮጵያ የሥልጣን ሳይሆን የአመራር ብቃት ክፍተት ሊያጋጥም እንደሚችል አንድ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኝ አስታወቁ ። በአለም አቀፉ የፀጥታ ጉዳዮች ጥናት ተቋም አጥኚ ዶክተር መሐሪ ታደለ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት በመለስ አለመኖር አገሪቱ የሥልጣን ክፍተት አያጋጥማትም እስካሁን የመረጋጋት ችግር እልታየባትምም ፣ወደፊት ግን የአመራር ብቃት ክፍተት ሊኖር ይችላል ። በፖለቲካው መስክ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ደግሞ ገዥው ፓርቲ የምክክር ና የስምምነት መድረኮችን ማዘጋጀቱ ጠቃሚ ይሆናል ብለዋል ። ላለፊት 21 አመታት ኢትዮጵያን በፕሬዝዳንትነትና በጠቅላይ ሚኒስትርነት ከመሩት ከአቶ መለስ ዜናዊ ህልፈት በኋላ የገዥው ፓርቲ የኢህአዲግ አመራር እንዴት ይቀጥላል ? ኢትዮጵያስ ከመለስ በኋላ ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ የምታገኘው ድጋፍና የሚኖራት ተቀባይነት ምን ይሆናል ? መለስስ በምን ይታወሳሉ የሚሉትና የመሳሰሉት ጥያቄዎች ማነጋገራቸውን ቀጥለዋል ። በአለምአቀፍ የፀጥታ ጉዳዮች ጥናት ተቋም ተመራማሪ ዶክተር መሐሪ ታደለ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአመራር ዘመናቸው በኤኮኖሚና ማህበራዊ መስኮች ለኢትዮጵያ አዳዲስ ውጤቶች ማሰገኘታቸው ይጠቅሳሉ ። በፖለቲካው መስክ ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይከተሉት የነበረው መርህ ብዙ ችግሮችና ቅሬታዎች ያስከተሉ እንደነበር ዶክተር መሐሪ ገልፀዋል ። ይም ሆኖ ሃገሪቱ መሠረታዊ እንቅስቃሴ ውስጥ እንድትገባ ያደረጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ነበሩ ብለዋል ። ከእንግዲህ በኋላስ የሚለው ሌላው ጥያቄአችን ነበር ። ዶክተር መሃሪ እንደሚሉት በተለይ አቶ መለስ ጥሩ አመራር ሰጥተው ውጤት አሳይተዋል ባሉት የኢኮኖሚ መስክ የታዩ ለውጦችን መቀጠል ከባድ ፈተና መሆኑን ይገልፃሉ ። በፖለቲካ መስክ ደግሞ አሁ

ከደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት የተሰጠ የሐዘን መግለጫ

የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ከድህነትና ኋላቀርነት ለማላቀቅ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በቅንነትና በታማኝነት አገራቸውን አገልግለው ከፍተኛ የለውጥ ተስፋ ያሳዩትን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕልፈተ ህይወት የሰማነው በታላቅ ድንጋጤና መሪር ሐዘን ነው፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አምባገነኑን የደርግ ስርዓት ለማስወገድ በተደረገው ትግል በመታገልና በማታገል ለሀገራችን ለውጥ ታላቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታላቅ መሪ ነበሩ፡፡ እንዲሁም ሀገራችን የህገ መንግስት ባለቤት እንድትሆንና በህገ መንግስቱና በህገ መንግስታዊ ስርዓቱ መሰረት ጠንካራ መንግስት እንዲኖራት ለማድረግ የታገሉ ግንባር ቀደም መሪያችን ነበሩ፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሀገራችን ለተመዘገበው እድገት መሰረት የሆኑ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን ነደፈው ተግባራዊ እንዲደረግ ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱና በነዚህ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች አማካኝነት ለተመዘገበው እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራቸው መሪም ነበሩ፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ፣ የፌዴራል ስርዓት እውን እንዲሆን ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ፣ ዛሬ የክልላችንና የሀገራችን ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ለተጎናፀፏቸው ራስን በራስ የማስተዳደርና በልማት አስተዋጿቸው ልክ የመጠቀም አቅጣጫ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራቸው መሪያችን በመሆናቸው የክልላችን ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች የዝንተ ዓለም ባለውለታ ናቸው፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሀገራችን ብቻ ሳይሆን በአፍሪካና በአለም አቀፍ ደረጃ የተለያዩ ችግር ፈቺ ሐሳቦችን በማመንጨትና በማፍለቅ ሀገራችንና አህጉራችን በአለም አቀፍ ደረጃ

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የቀብር ስነሰርዓት ተፈጸመ

Image
አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 17፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈፀመ ። በቀብር ስነ ሰርዓቱ ላይ  ተጠባባቂ  ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማሪያም ደሳለኝን ጨምሮ ሚኒስትሮች ፣  የተለያዩ አገራት አብያተ ከርስቲያናት መሪዎች ፣ አምባሳደሮችና  በሺዎች የሚቆጠሩ  የእምነቱ ተከታዮች ተገኝተዋል ። በስነ ስርዓቱ ላይ  አቶ ሀይለማሪያም ብፁዕ  ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አገሪቱን ከድህነት ለማላቀቅ በተደረገው ጥረት ከፍተኛ ተሳታፊ የነበሩ አባት ናቸው ብለዋል ። በቤተ ክርስቲያኗም ሆነ በአገሪቱ በተከናወኑ የልማት ስራዎች ከነበራቸው ተሳትፎ ባለፈ በዓለም አብያተ ክርስቲያናት  ዘንድ ያላቸውን ተሰሚነት በመጠቀም የአገራቸውን  በጎ ገፅታ ያሳወቁ ብልህ አባት ነበሩ ሲሉም ገልጸዋቸዋል። የአቡነ ጳውሎስን የበጎ አድራጎት ተግባር ተሳትፎን  ያስታወሱት አቶ ሀይለማሪያም ፥ በኤች አይ ቪ /ኤድስ ወላጆቻቸውን ያጡ ህፃናትን በመደገፉ እንዲሁም የቫይረሱን ስርጭት በመከላከሉ ረገድ ያከናወኗቸው ስራዎች የሚያስመሰግናቸው ነው ብለዋል ። የዓለም አብያተ ክስርስቲያናት ምክር ቤት ፀሃፊ በበኩላቸው የምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት የነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ  ጳውሎስ ለዓለም ሰላም የሰሩና የአመራር ብቃታቸውንም ብዙዎች አርዓያ የሚያደርጉት መሆኑን ተናግረዋል ። በ76 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት አቡነ ጳውሎስ ከ1985 ዓመተ መህረት ጀምሮ የኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አምስተኛ ፓትሪያሪክ  ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል ። በ1999 ዓመተ ምህረት በብራዚል በተካሄደው የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ጉባኤ ላይም የምክር ቤቱ

በተጠናቀቀው በጀት አመት ከቀረቡለት 1ሺህ 4 መቶ 11 የክስ መዛግብት ለ1ሺህ 3መቶ 90 ውሣኔ መስጠቱን በሲዳማ ዞን የአለታ ወንዶ ወረዳ ፍርድ ቤት ገለፀ፡፡

የወረዳው ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ወንድሙ ቂጤሶ እንደገለተጹት  በተጠናቀቀው በጀት አመት ጽህፈት ቤቱ ከቀረቡለት 1ሺህ 4 መቶ 11 የክስ መዛግብት ውስጥ 1 ሺ 3 መቶ 90 ዎቹ ውሣኔ መሰጠቱንና ቀሪዎቹ 21 መዛግብት ደግሞ ለቀጣዩ አመት ማስተላለፉን ተናግራል፡፡ ፍትህ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ከማድረግ አንፃር የአመቱነ አፈፃፀም 98 ነጥብ 5 ከመቶ ማድረሱን ጠቅሰው፤ ለቀጣዩ አመት መቶ በመቶ ለማድረስ ጠንክረው እየሰሩ አንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡ አርሶ አደሩ ከልማት ሥራው ሣይለይ ፍተህ በአከባቢው ያገኘ ዘንድ በተቋቋሙ 4 ማዕከላት ፍትህ በመስጠት አበረታች ውጤት የተመዘገበ መሆኑን የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ በአዲስ አመት ወደ 6 ለማሣደግ ታቅዶ እየተሠራ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ አርሶ አደሩ በህገ ወጥ ደላላዎች ይገጥመው የነበረውን የግንዛቤ እጥረት ለመቅረፍ ጧት ከችሎት በፊት በባለሙያዎች ትምህርት እየተሰጠ እንዳለ ገልፀዋል፡፡የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት እንደገለጸው፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/14NehTextN904.html

በሲዳማ ዞን የአለታ ወንዶ ወረዳ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በተጠናቀቀው በጀት አመት ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብቡን አስታወቀ፡፡

ጽህፈት ቤቱ በአመቱ ለመሰብሰብ ያቀደው 6 ሚሊዮን ብር ሲሆን  ከ9 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ሊሰበሰበብ መቻሉን የወረዳው ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምስራቅ በቴ ገልፀዋል ፡፡ የአመቱ እቅድ ክንውን አፈፃፀም 98 ነጥብ 2 ከመቶ መሆኑንና ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም የ3 ሚሊዮን 61ዐ ሺህ 196 ብር ብልጫ ማሳየቱን ኃላፊው አስረድተዋል ፡፡ ገቢው ሊሰበሰብ የቻለው ከቀጥተኛና ቀጥተኛ ካልሆኑ ገቢዎች እንዲሁም ከልዩ ልዩ ገቢዎች መሆኑን አብራርተዋል ፡፡ ለገቢው መጨመር የግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ግብር የመክፈል ግንበዛቤ እያደገ መምጣት፣ የጽህፈት ቤቱ ሠራተኞች የሥራ ተነሳሽነት መፈጠርና የወረዳው መስተዳደርና ባለድርሻ አካላት ከገቢ ሰብሳቢው ጽህፈት ቤት ጋር የተቀናጀ ሥራ በማከናወናቸው መሆኑን ኃላፊው ጠቁመዋል ፡፡ በቀጣይ አዳዲስ የገቢ ምንጮችን በማፈላለግ የተጀመረውን የ5 ዓመት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ስኬት በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ አቶ ምስራቅ መናገራቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ዘግቧል ፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/14NehTextN604.html

የደቡብ ክልል የሚገኙ የተለያዩ መስሪያ ቤቶች በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸውን መሪር ሀዘን ገለፁ

  አዋሳ ነሐሴ 17/2004 በደቡብ ክልል የሚገኙ የተለያዩ መስሪያ ቤቶችና ተቋማት አመራር አባላትና ሰራተኞች በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸዉን ጥልቅ ሀዘን እየገለጹ ነዉ ። የደቡብ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ፣የክልሉ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ፣የኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋምና የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ሠራተኞች፣ መምህራንና ተማሪዎች በታላቁ መሪያችን ሞት ጥልቅና መሪር ሀዘን ተሰምቶናል ብለዋል ። ቢሮዎቹና ተቋማቱ ባስተላለፉት የሀዘን መግለጫ ላይ እንዳስታወቁ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከወጣትነት እድሜያቸዉ ጀምሮ እስከ እለተ ሞታቸው የኢትዮጵያ ህዝብ ከድህነት ተላቆ በእድገትና ብልጽግና ጎዳና እንዲጓዝ ታላቅ ራእይ ሰንቀዉ የተነሱ ቆራጥና አስተዋይ መሪ ነበሩ ብለዋል ። የየቢሮዎችና የተቋማቱ ሰራተኞች ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የአመራር ጥበባቸውን በመጠቀም ኢትዮጵያን በልማት ለማሳደግ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ አሁን ለደረሰንበት የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የዲሞክራሲ ስርዓት ያበቁ ታታሪና ብልህ መሪ እንደነበሩ አስታዉቀዋል ። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ "ለመጪው ትውልድ ዕድገት፣ ብልፅግናና ልማትን እንጂ ድህነትን አናወርስም "በማለት በቆራጥነትና በታላቅ ኃላፊነት መንፈስ ሲሰሩ የቆዩ የለውጥ ሐዋሪያ ናቸው ሲሉ የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ገልፀዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ኢትዮጵያ በአለም ከምትታወቅበት የተመፅዋችነትና የረሃብ ታሪክ እንድትላቀቅ በዓለም ትልቅ የልማት ተስፋ ሆነው ከሚታዩ የዓለም አገራት ተርታ እንድትሰለፍ ያደረጉ ጀግናና በሳል መሪ ነበሩ ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የእርሳቸዉን በጎ ተግባር በመከተል ብቃት ያለው የልማት ሠራዊት መሆን የሚችል በሁሉም መስክ የሰለጠነ የሰው

የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ዕረፍት አስመልክቶ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች የሰጡት አስተያየት

Image
በመገናኛ ብዙኅን የሰማሁት ነገር እጅግ ልብ የሚነካና የሚያሳዝን ነው፡፡ የተከበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ትልቅ ራዕይና አቅም የነበራቸው መሪ ነበሩ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥም ከትጥቅ ትግሉ ጀምሮ ይኼ ነው የማይባል ጊዜያቸውን መስዋዕት አድርገው፣ አምባገነኑን የደርግ ሥርዓትን መክቶ ማሸነፍ የቻለ ፓርቲ መመሥረት የቻሉ ግለሰብ ናቸው፡፡ ከዚያም በኋላ በኢትዮጵያ ውስጥ ይህ ነው የማይባል የፖለቲካና የኢኮኖሚ መነቃነቅን የፈጠረ አቅም የነበራቸው ግለሰብ ነበሩ፡፡ ወደፊትም በኢትዮጵያ ውስጥ ረጅም ርቀትን ለመሄድ የሚያስችል አቅም የነበራቸው ግለሰብ ናቸው ብዬ ነው የማምነው፡፡ ለኢትዮጵያ ካቀዱትና ይዘውት ከተነሱት ዓላማ አኳያ መታጣታቸው እጅግ በጣም አሳዛኝ ነው፡፡ በተረፈ እንደ አባት ደግሞ ለቤተሰቦቻቸው እጅግ ትልቅ እጦት ነው፡፡ ለአፍሪካ ማኅበረሰብም አፍሪካን በማስተሳሰርና አንድነትን በማምጣት፣ በልማት መስመር ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ ቀላል የማይባል ሚና የተጫወቱ ግለሰብ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ ስናያቸው እንደ አገር መሪ ይዘውትና ሰንቀውት የተነሱት ነገር ረጅም ርቀት የሚወስደን መሆኑ ምንም ጥያቄ የለውም፡፡ ወደፊትም ቢሆን በጀመሩት ነገር ላይ ተጨማሪ ሥራ ለመሥራት አቅም የነበራቸው ግለሰብ ነበሩ፡፡ እስከዛሬ ድረስ የሰበሰቡት ዕውቀት፣ ያከማቹት ግንዛቤና ተሞክሮ ወደሚቀጥለው ኃይል ተላልፎ አለማየትም ትልቅ እጦት ነው፡፡ በቀጣይ የሚጠበቀው ነገር ከኢሕአዴግ ነው፡፡ ሕገ መንግሥቱ ላይ በሰፈረው መሠረት ኢሕአዴግ የሥልጣን ሽግግሩን በአግባቡ መወጣት አለበት ብዬ አምናለሁ፡፡ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ በሆነ መንገድ፣ በማያሻማና በሚታይ ሁኔታ መሆን አለበት እላለሁ፡፡ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ተቀራርቦ አገርን በማልማትና በማሳደግ ሒደት ውስጥ ቀዳዳ እንዳይኖረው

‹‹መለስን መተካት ከባድ ነው››

ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ‹‹የተጀመረው ልማት እንዲቀጥል አደራ›› የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ኑዛዜ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ሕልፈት ምክንያት በተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትርነት እንዲሠሩ ኃላፊነት የተጣለባቸው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ ‹‹መለስን መተካት ከባድ ነው›› አሉ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ለማስቀጠል ግን አዲሱ አመራር ዝግጁ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ትናንት አመሻሽ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት አቶ ኃይለ ማርያም፣ ‹‹ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እንደ ሻማ ቀልጠዋል፤›› ብለዋል፡፡ ላለፉት 38 ዓመታት በሰው ልጅ ታሪክ የሚጠቀስና በብቃት የሚፈለግባቸውን መሥራታቸውን ገልጸዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕልፈትን ተከትሎ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጫፍ እስከ ጫፍ ከፍተኛ ሐዘን እንደተሰማው ተናግረው፣ ‹‹የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዘለዓለም በታሪክ ሊዘክራቸው የሚገባ መሪ ነበሩ፤›› ብለዋል፡፡ በእሳቸው አመራር የተገኘው ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማስቀጠል አዲሱ አመራር ቃል ኪዳን የሚገባበት ፈታኝ ጊዜ መሆኑን በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡ ‹‹በእሳቸው አመራር የተጀመረው የአመራር መተካካት ሒደት አይደናቀፍም ወይ?›› በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ ሒደቱ በጥናት ላይ የተመሠረተና በኢሕአዴግ ውስጥ ሙሉ መተማመን ላይ የተደረሰበት ስለሆነ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ መሞት የሚደናቀፍ አይሆንም በማለት፣ በእሳቸው ጊዜ የተጀመረው የአዲሱ ትውልድ የአመራር መተካካት በብቃት እንደሚከናወን አስረድተዋል፡፡ በማገገም ላይ ሳሉ ከአራት ቀናት በፊት ኢንፌክሽን አጋጥሟቸው ሕይወታቸው አደጋ ላይ እስኪወድቅ ድረስ በስልክ ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ጋር በተደጋጋሚ መ

የሃዋሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራር፣ መምህራንና ተማሪዎች በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ድንገተኛ ሞት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለፀ

አዋሳ ነሐሴ 16/2004 የሃዋሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራር፣ መምህራንና ተማሪዎች በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለሰ ዜናዊ ሞት የተሰማቸዉን ጥልቅ ሀዘን ገለፁ፡፡ ኮሌጅ አመራር፣ መምህራንና ተማሪዎች ባስተላለፉት የሀዘን መግለጫ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጠንካራ፣ ስራ ወዳድና የዓላማ ጽናት የነበራቸዉ ቆራጥ መሪ በመሆናቸው ያቀዱት ዕቅድ ያለሙት ዓላማ ሁሉ ውጤት ሊያስገኝ ችሏል፡፡ ዜጎች በራስ በመተማመን በአብዛኛው በቴክኒክና ሙያ በመሰማራ ሥራ እየፈጠሩና ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ በተቀመጠው አቅጣጫ ብዙ ዎች ሃብትና ንብረት በማፍራት የሀገር ኩራት እስከመሆን ደርሰዋል ብለዋል ፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ከድህነት እንዲላቀቅ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ያደረጉት ያላሰለሰ ጥረት ውጤት በመሆኑ መልካም ስራቸዉ ህያዉ ሆኖ እንደሚኖር የኮሌጅ አመራር፣ መምህራንና ተማሪዎች አስታዉቀዋል ። ታላቁ መሪያችን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ለኢትዮጵያ ሀዝብ እድገትና ብልጽግና የሚበጁ መሰረቶችን የጣሉ ብሩህ አዕምሮና አርቆ አሳቢ መሪያችንን በሞት መነጠቃችን ጎድቶናል፡ ብለዋል ። የእሳቸው ዕቅድና ስትራቴጂ ተከትለን ለአገራችን እድገትና ብልጽግና በበለጠ ጥንክረን ለመስራት ዝግጁ መሆናችንን አየገለፅን ለቤተሰቦቻቸው ለወዳጆቻቸውና ለኢትዮጵያ ህዝብ መፅናናትን እንመኛለን ብለዋል ፡፡

Ethiopian Succession Battle May Test Stability Of Key U.S. Ally,Potential successors in addition to Hailemariam include the State Minister for Foreign Affairs Berhane Gebrekristos from Meles’s Tigray People’s Liberation Front, or TPLF; Amhara Regional State President Ayalew Gobeze; and Health Minister Tewodros Adhanom Gebreyesus, who is a TPLF executive committee member, said Terrence Lyons

By  William Davison  -  Aug 21, 2012 Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi’s death may cause a succession battle that could test the stability of one of  Africa ’s fastest-growing economies and a key ally in the U.S.’s war against al-Qaeda. The 57-year-old premier died Aug. 20 from an infection after recuperating at a hospital in an undisclosed location from an unspecified illness. Deputy Prime Minister Hailemariam Desalegn is serving as acting prime minister. Competition to succeed Meles may fracture the unity of the ruling Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front and embolden opposition groups frustrated by years of government suppression, said analysts including Jennifer Cooke, director of the Africa Program at the Washington-based Center for Strategic and International Studies. That may jeopardize a state-driven program that generated average economic growth of 11 percent over the past seven years, while placing at risk  Ethiopia ’s role as a peacekeeper in the H