Posts

ሠራተኛው ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን ጠንክሮ መሥራት አለበት

Image
አዋሳ ግንቦት 05/2005 ሠራተኛው የስራ ባህሉን በማሻሻል በታታሪነት በመስራት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን ጠንክሮ መሥራት እንዳለበት ተገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማብራት ኮንፌዴሬሽን 50 ዓመት የወርቅ ኢዩቤል ክብረ በዓሉን ትላንት በሀዋሳ ከተማ በፓናል ውይይት አክብሯል፡፡ የርዕሰ መስተዳድሩ ስተዳድሩ ተወካይ አቶ ታመነ ተሰማ ትናንት በፓናል ውይይቱ መክፈቻ ላይ እንደገለጹት ሠራተኛው የስራ ባህሉን በማሻሻል በታታሪነትና በዓላማ ፅናት በመስራት በአለም ገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን ጉልበትና ዕውቀቱን አቀናጅቶ ጠንክሮ መሥራት አለበት፡፡ ኢሠማኮ የግል ተቀጣሪ ሰራተኞች የማህበራዊ ዋስትና እንዲያገኙና ሀገሪቱ ከግብር መር ወደ እንዱስትሪ መር እንደድትሸጋገር በማድረግ በኩል ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ከሳሁን ፎሎ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ሰራተኞች ያበረከቱአቸውን ሀገራዊ አስተዋጽኦ የመዘከር፣ አሰሪና ሰራተኛ ተግባብተው በአንድ መንፈስ እንዲንቀሳቀሱ የማነሳሳትና ሁሉም ወገን ተጠቃሚ የሚሆንበት ምቹ ሁኔታን የመፍጠር አላማ ያነገበ ነው ብለዋል፡፡ ሠራተኛው ጉልበትና ዕውቀቱን ሳይቆጥብ የህዳሴውን ግድብ ከግብ ለማድረስ እያደረገ ያለው ያላሰለሰ ጥረት የሚያኮራ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በበዓሉ ላይ በሀዋሳና አካባቢዋ የሚገኙ ሰራተኞች አሰሪዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡ Sources: Ena

አስደንጋጮቹ የሙስና ምልክቶች

በአማን ንጋቱ በሁሉም መሥሪያ ቤቶች ግድግዳ፣ በር፣ የማስታወቂያ ሰሌዳ አንዳንዴም በውስጥ ክፍሎች የተደረቱ ጽሑፎች ይታያሉ፡፡ ቢነበብም ባይነበቡም አንዱ በሌላው ላይ እየተደራረቡ ጽሑፎች ይለጠፋሉ፡፡ አሥራ ሦስት ገደማ ፍሬ ነገሮችን የያዘው “የሥነ ምግባር ደንብ መርሆዎች” የሚለው ርዕስ በየቦታው ጎልቶ ይታያል፡፡ እንደ ቅንነት፣ ታማኝነት፣ ግልጽነት፣ ሐቀኝነት ያሉት የአብዛኛዎቹ መርሆዎች ማጠንጠኛቸው፣ “ሙስና፣ ጉቦና መድልኦን መፀየፍ” እንደሆነ ከጽሑፎቹ መገንዘብ ይቻላል፡፡ ይሁንና መርሆዎቹ ከወረቀት ጌጥነት ባለፈ ያመጡት ለውጥ ምንድን ነው? የሚል ጥያቄ መነሳት አለበት፡፡ የለውጥ ሥራዎች ተግባራዊነት፣ የድርጅት ግምገማ መጠናከር (ከብዛቱ አንፃር ትግል ደክሟል የሚሉ የኢሕአዴግ ሰዎች አሉ) የሕጉ መሻሻልና የማስቀጣት አቅም መጨመር ዕውን ሙስናን ቀንሶታል ወይስ ተባብሷል በማለት የሚጠይቁ በዝተዋል፡፡  አቶ ጀማል ያሲን የሥነ ዜጋና ሥነ ምግባር መምህር ናቸው፡፡ በትምህርት ሥርዓቱ የሥነ ዜጋና ሥነ ምግባር ትምህርት ቢቀረፅም ሳይሠሩ የመክበር ዝንባሌው ሥር የሰደደ በመሆኑ በቀላሉ የሚነቀል ነቀርሳ አይደለም ይላሉ፡፡ “ሲሾም ያልበላ…” ከሚለው ተረት “የኮንትሮባንድ ፈታሽ” ወይም “የመርካቶ ትራፊክ ያድርግህ” እስከሚለው ምርቃት ድረስ ሳይሠሩ የመክበር አስተሳሰብ የተንሰራፋ እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡ ቀስ በቀስ እየገነነ የመጣው ከመንግሥታዊ መዋቅር ባለፈ በሃይማኖት ተቋማትና በሲቪክ ማኅበራት ሳይቀር የሚታይ ጉቦ የመጠየቅ ፍላጎት ምንጩም ይኼው ነው፡፡  ዛሬ በትምህርትና በሕክምና ተቋማት ብቻ ሳይሆን በቀብር ሥፍራ ሳይቀር ሕግ ከሚያውቀው ክፍያ ውጪ “መወሸቅ” ተለምዷል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች ደግሞ፣ የነፃ ገበያና ኮሚሽን (ኤጀንት) ከሥራ መስክነት

የምርት ገበያው ደካማ አሠራር ቡና አቅራቢውን እያኮላሸው መሆኑ ተገለጸ

Image
የምርት ገበያው ደካማ አሠራር ቡና አቅራቢውን እያኮላሸው መሆኑ ተገለጸ የጽሑፍ መጠን       ኢሜይል   0 አስተያየት шаблоны RocketTheme Форум вебмастеров የኢትዮጵያ ምርት ገበያ አሠራር ችግር እየፈጠረባቸውና ለከፍተኛ ኪሳራ እየዳረጋቸው መሆኑን የቡና አቅራቢዎች በተደጋጋሚ ሲገልጹ መቆየታቸው የሚታወቅ ሲሆን በተለይ የሲዳማ ቡና አቅራቢዎች ማኅበር ለችግሩ መፍትሔ እንዲሰጠው ጥያቄ ማቅረቡ ታውቋል፡፡ ማኅበሩ በቅርቡ በሐዋሳ ከተማ ባካሄደው ስብሰባ፣ በሐዋሳ የሚገኘው የምርት ገበያው ማዕከል፣ አደረሰብን ያሉትን ችግር በዝርዝር በማስቀመጥ፣ ይህንን ችግር እንዲፈታላቸው ለመንግሥት አቤት ብለዋል፡፡  በስብሰባው ወቅት እንደተገለጸውና መንግሥት እንዲያውቅልን በማለት በጽሑፍ ያዘጋጁት መረጃ እንደሚያሳየው፣ ችግሩ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጀምሮ የተዛባ የቡና ጥራት ደረጃ አሰጣጥን የሚያጠቃልል ነው፡፡ የቡና ደረጃ አሰጣጥ ላይ ያለው የተዘበራረቀ አሠራር ከአቅማችን በላይ ሆኗል የሚሉት የማኅበሩ አባላት፣ ደረጃውን ጠብቆ የተዘጋጀ ቡና በአንዱ የምርት ገበያው ማዕከል ባለሙያዎች የተሰጠው ደረጃ በሌሎች ማዕከሎች ግን ደረጃውን አልጠበቀም ተብሎ ይጣልባቸዋል፡፡  ባለፉት ሁለት ወራት የሐዋሳው የምርት ገበያ መጋዘን ጥበት አጋጥሞታል በመባሉ ወደ አዲስ አበባ የላኩት ቡና፣ ሐዋሳ ላይ ደረጃ አምስት ተብሎ አዲስ አበባ ላይ ግን በጥራቱ የደረጃ ሁለት ማዕረግ እንደተሰጠ የተመደበ ሲሆን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡  እንዲህ ባሉ አግባብ ያልሆኑ አሠራሮች ምክንያት የቡና ላኪዎች ጉዳት ላይ እየወደቁ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ በዚህም ችግር አንድ ቡና አቅራቢ ድርጅት በአንድ መኪና በግምት ከ80 እስከ 100 ሺሕ ብር እየከሰረ

በተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም የአካባቢያዊ የዘር ቢዝነስ ፕሮጀክት 3 (LSB) እንቅስቃሴ

Image
ዶ/ር ሁሴን መሀመድ እባላለሁ፤በመምህርነት (በአሶሼትፕሮፌሰር ማዕረግ)፤ በዕፅዋት ማዳቀልና ዝርያ በማውጣት በአሁኑ ወቅት ደግሞ ከመምህርነት በተጨማሪነት በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም አስተባባሪ በመሆን እያገለገልኩ እገኛለሁ፡፡ የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት በጣም ሰፊ ፕሮግራም ነው፡ የዘር ዘርፍ ደግሞ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ያሳድጋሉ ከምንላቸው አስፈላጊ ግብአቶች አንዱ ነው፡፡ በፕሮግራሙ ዋና አላማችን ዓለም አቀፍ ሰብል ዝርያ አባዢ ድርጅቶችን፤ ኢትዮጵያዊና ገና በመጠናከር ላይ ያሉ የግል የዘር አባዢዎችን በተጨማሪም ተደራጅተው ዘርን አባዝተው የሚያቀርቡ የአርሶ አደር ማህበራትንና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን አቀናጅቶ ለእድገታችን ማነቆ ሆኖ የቆየውን የዘር ዘርፍ ችግርን ለመፍታት ዘርን በጥራትና በብዛት በማምረትና በማቅረብ በሀገራችን ውስጥ የጀመርነውን ፈጣን እድገት አስተማማኝ ለማድረግ ነው ፡፡ የዘር ዘርፍን ለማጠናከር የISSD ፕሮግራም የአርሶ አደር የዘር ብዜትና ግብይት ማህበራትና የግል የዘር አባዢዎችን በመደገፍ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የተመሰከረለት ዘርን (Certified Seed) መጠበቅ፤ ጥራታቸውን የጠበቁ አራቢ፤ መስራችና ቅድመመስራች ዘሮችን በምርምር ማዕከላት ደረጃ በጥራት እንዲመረቱና የአቅም ማጎልበት ስራንም ለመስራት መሰረታዊ የዘር ዘርፍ ችግርን የሚያጤን ኮሚቴ (Core Group) ከተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም፤ ከክልል ግብርና ቢሮ፤ መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች (NGO)፤ ከደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅትና፤ ከደቡብ ግብርና ምርምር ማዕከል በተወጣጡ አባላት ተቋቁሞ በዘርፉ ያሉትን ችግሮች ነቅሶ በማውጣት ለእነኚህ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት እየሰራን እንገኛለን፡፡ ቀደም ብሎ የዘርፉ መሰረታዊ ች

ዩኒቨርስቲው ሶስት አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች በድህር ምረቃ ደረጃ ሊከፍት ነው

Image
ሃዋሳ ግንቦት 03/2005 የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በ2006 የትምህርት ዘመን በድህረ ምረቃ ደረጃ አዳዲስ ፕሮግራሞችን ለመክፈት እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ፡፡ ዩኒቨርሰቲው የቅበላ አቅሙን ለማሳደግም 2 ቢሊዮን ብር በሚጠጋ በጀት የማስፋፊያ ግንባታ በማካሄድ ላይ ነው፡፡ ዩኒቨርስቲው የሚከፍታቸው አዳዲስ ኘሮግራሞች በጋዜጠኝነትና ማስ ኮሚኒኬሽን፣ በሶሻል ሳይኮሎጂ እንዲሁም በጎልማሶች ትምህርትና የህብረተሰብ ልማት ዘርፎች ነው፡፡ ለሶስቱ አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች የተቀረጹትን ስርዓተ ትምህርቶችን ለማዳበር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ በተዘጋጀው መድረክ ላይ በዩኒቨርስቲው የሶሻል ሳይንስና ሂውማኒቲስ ኮሌጅ ዲን ዶክተር ንጉሴ መሸሻ እንዳስታወቁት በድህረ ምረቃ ደረጃ የሚከፈቱት እነዚህ ፕሮግራሞች በየትምህርት ዘርፉ ሀገሪቱን ወደተሻለ አቅጣጫ እንድትጓዝ የሚያስችሉ ብቁና ተወዳደሪ ምሁራን ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጾኦ አላቸው፡፡ በተለይ በጋዜጠኝናትና ማስ ኮሚኒኬሽን የስልጠና መስክ የዕድገትና የፖለቲካ ተግባቦት ፣ የማስታወቂያና የህዝብ ግነኙነትን ሲያካትት በሶሻል ሳይኮሎጂ ዘርፍ ደግሞ ወደፊት በሀገሪቱ ስለሚኖረው የማህበረሰባዊ ስነልቦና እና ሊከሰቱ የሚችሉ ችግሮች በማጥናት ብሎም ዜጎች በትክክለኛው መንገድ እንዲገዙ ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የጎልማሶች ትምህርትና የህብረተሰብ ልማት ዘርፍም በሀገሪቱ ያልተማሩ ዜጎችን ለማብቃት የጎልማሶች ትምህርት ከማህበረሰብ እደገትና ልማት ጋር አብሮ ለማስኬድ የሚስችሉ ብቁ ሙሁራን ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጸኦ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በፈጣን የእድገት እንቅስቃሴ ላይ የሚገኘው የሀዋሳ ዩኒቨርሰቲ ሀገሪቱ በምትፈልገው የዕድገት ጎዳና እንድትጓዝ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት ጠንክረው እየሰሩ መሆናቸው ዶክተር ንጉሴ አመልክ