Posts

ሕዝብ ለመንግሥት የቤት ሥራ ሰጥቷል ተግባራዊ ምላሽ ይጠበቃል!

ውል ክፍል መሄድ ሳያስፈልግና ቃለ ጉባዔ መፈራረም ሳይጠይቅ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመንግሥት የቤት ሥራ ሰጥቷል፤ አደራ አቅርቧል፡፡ ተግባራዊ አዎንታዊ ምላሽም ከመንግሥት ይጠብቃል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን በሚያስገርም፣ በሚያስመካና ታሪካዊ በሆነ ሁኔታ ከልብ ገልጿል፡፡ ታሪክም ለዘለዓለም ሲዘግበው ይኖራል፡፡ በክብር መዝገብ አስፍሮታል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን ሐዘኑን ብቻ አይደለም የገለጸው፡፡ የተጀመረውን የልማት ሒደት ዳር ለማድረስም ቃል ገብቷል፡፡ አሁንም በሕገ መንግሥታችን የሰፈሩትን መብቶችና ጥቅሞች እውን ለማድረግና የኢትዮጵያን ራዕይ ዳር ለማድረስ ዝግጁነቱን ገልጿል፡፡ በእንባም፣ በቃላትም፣ በፀሎትም፣ በሠልፍም፡፡ ሕዝብ መንግሥትን ‹‹ምራ እንከተልሃለን›› ብሏል፡፡ አደራውና የቤት ሥራውም ይኼው ነው፡፡ መንግሥት ይህንን የሕዝብ አደራና የቤት ሥራ በተገቢው መንገድ በተግባር ለመመለስ መንቀሳቀስ ይጀምር፡፡ መንግሥት ይህን የሕዝብ አደራና የቤት ሥራ የሚመልሰው እንዴት ነው? ለመመለስስ ይችላል ወይ? ገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግና መንግሥት ይህን የሕዝብ አደራና የቤት ሥራ በሚገባ ከተገነዘቡትና መመለስ አለበት ብለው ካመኑበት ተገቢ ምላሽ ለመስጠት ምንም አያዳግታቸውም፡፡ ይቻላል፡፡ ለመመለስ ግን የሚከተሉትን መፈጸም አለባቸው፡፡ 1.    ቀጣይነት ሕገ መንግሥቱን መንግሥትም እንደ መንግሥት ኢሕአዴግም እንደ ገዥ ፓርቲ ያመኑበትና የተቀበሉት ብቻ ሳይሆን፣ እነሱ ሥልጣን ይዘው ባሉበት ጊዜ በራሳቸው ተነሳሽነት እውን የሆነ ነው፡፡ ስለሆነም ለቀጣይነቱ ችግር የለውም፡፡ የአምስት ዓመቱ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድም ባለው መንግሥትና ገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ የታቀደና የፀደቀ ነው፡፡ ለተግባራዊነቱ ችግር የለ

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚህ ዓለም በሞት መለየት ከተሰማ ጀምሮ መግለጫ ከሰጡት መካከል በሲዳማ ዞን ስር የሚገኙ የንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ፣ መንገዶችና ትራንስፖርት መምሪያ፣ የዳሌ ወረዳ አስተዳደር በሃዋሳ ከተማ የዳካ ቀበሌ ታዳጊ ተማሪዎች ህብረት፣ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ እንዲሁም የሀዲያ ዞን ንግድና ኢንዲስትሪ ልማት መምሪያ ይገኙበታል፡፡

ባለራዕይና የዘመናችን ታላቁ መሪ መለስ ዜናዊ ሁሉአቀፍ እውቀትና የመምራት ብቃት ያላቸው በሳል መሪ ነበሩ ብለዋል፡፡ በተመሳሳይም በይርጋዓለም ከተማ የሠላም አንድነት አረጋዊያን ማህበር የተስፋ ራዕይ አውራጅና ጫኝ ማህበር፣ ራይስ ኢንጀነሪንግ ኒያላ ሞተርስ፣ ሲዳማ ቡና አቅራቢዎች ማህበር፣ ፖራዳይስ ሆቴል፣ ይርጋዓለም ኮንስትራክሽንና  ኦሲስ ሆቴል ውስጥ የሚገኙ ሠራተኞች፣ ሃላፊዎቹና ባለቤቶቹ የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል፡፡ መሪያችን የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ አሌኝታ  የሆኑ ታላቅ ሰው ነበሩ ያሉት መግለጫ  ሰጪዎቹ በእሳቸው የተጀመሩትን እቅዶች ተግባራዊ በማድረግ ስራቸውን ከመቃብር በላይ ሲታወሱ እንዲኖሩ እናደርጋለን ብለዋል፡፡ በተለይም ይህን የሰነቁትን ዓላማ ወጣቱ ትውልድ በደንብ ተገንዝቦት በጋራ የመረባረቡን ሃላፊነት እንዲወጣ አደራቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብና ቤተሰቦቻቸውን መፅናናትን እንመኛለን ብለዋል፡፡

የሲዳማ ዞን ነዋሪዎች መንግስት በዞኑ የምፈጸመውን የሰብኣዊ መብት ረገጣ፡ እስር እና እንግልት እንዲያቆም ጠየቁ፤ በመንግስት ላይ ህዝብን በማነሳሳት በምል የታሰሩ ግለሰቦች ያለ ምንም ቅድሜ ሁኔታ እንዲፈቱ ኣሳሰቡ።

የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ሪፖርተሮች ተዘዋውረው ያኗገራቸው የዞኑ ነዋሪዎች እንደተናገሩት፤ መንግስት በሰበብ ኣስባቡ የተለየ ኣመለካከት እና ኣስተሳሰብ የምያራምድ ግለሰቦችን በኣስፈለገው ጊዜ እና ወቅት የተለያዩ ስሞችን በመስጠት በማስር ላይ ነው። በሃዋሳ ከተማ ሌዊ ሆቴል ሲዝናኑ ያገኘናቸው ካላ ጌታሁን ሳርምሶ የተባሉ በከተማዋ የኣዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ነዋሪ እንደተናገሩት፤ መንግስት በተለያዩ ጊዚያት በተለይ ከክልሉ ባለስልጣናት ፖለቲካዊ ኣመለካት የተለየ ያለ ኣመለካከት ያላቸውን ግለሰቦች ማሰሩ የተለመደ ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰው በኣሁኑ ጊዜ በተለይ ከሲዳማ የፊቼ በዓል ማግስት ጀምሮ በርካታ ሰዎች ህዝብን በመንግስት ላይ በማነሳሳት ተከሰው ታስረዋል። ግለሰቦች የመሰላቸውን ፖለቲካዊ ሆነ ማህባራዊ ኣመለካከትን ያለ ምንም ገደብ እንዲያራምዱ በምፈቅድ ህገ መንግስት ባለባት ኣገር ግለሰቦች የተለየ ኣመለካከት ስላላቸው ብቻ ስብኣዊ መብታቸው መጣሱ ኣግባብነት የለውም ብለዋል። ወጣት ንቆዲሞስ ኣየለ የተባለ በሃዋሳ ከተማ የባጃጂ ታክሲ ሽፌር በበኩሉ፤ የሲዳማ ክልል ይገባኛል ጥያቄ በተመለከተ ህዝባዊ ንቅናቄ  ከተጀመረ ወዲህ በተለይ ወጣቶች  በመንግስት የጸጥታ ሰዎች ማስፈራሪያ እንደምደርሳቸው ገልጿ፤ ለህዝቡ ጥያቄ ኣግባብነት ያለውን ምላሽ መስጠት እንጂ ሰዎችን ማስር እና ማንገላት መፍትሄ ኣይደለም ብለዋል። ካላ ዘርሁን ናራሞ የተባሉ በተለምዶ ስሙ ሊዝ ሰፈር በምባለው ኣከባቢ መንገድ ላይ ሲጓዙ ያገኘናቸው የሃዋሳ ከተማ ነዋሪ፤ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሃዋሳ ከተማ ብሎም በሲዳማ ዞን ወረዳዎች ውስጥ ግለሰቦች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ከመኖሪያ ቦታቸው እና ከስራ ገበታቸው እየተያዙ እንደምታሰሩ ጠቅሰው፤ ግለሰቦች በተጠረጠሩት ጉዳይ ላይ

የቡና ዋጋ ቅናሽ ማሳየት እያነጋገረ ነው

Image
ቃልዲ በኢትዮጵያ ምድር የገዘፈ ታሪክ ባለቤት ነው፡፡ በዘጠነኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ ይሆናል። ከከፋ መንደር ፍየሎች ጥዑም ፍሬን አገኙ። የመንጋው እረኛ ብላቴናው ቃልዲ ከዛን ዘመን ጀምሮ ስሙ በታሪክ ማኅደር ሰፈረ። ምክንያት የሚያግዳቸው ፍየሎች ለሀገሬውና ለዓለም ሕዝብ ቡናን በማሳወቃቸው ነው። ምስጋና ለእነርሱ ይሁንና ይኸው ዛሬም ድረስ ኢትዮጵያ ከጥዑም ቡናዋ እረኛው ቃልዲም ከታላቅ ስሙ ጋር ተቆራኝተው ለዘመናት መዝለቅ ችለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ካሉ ሰባት ታዋቂ ቡና አምራች ሀገራት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉርም በዘርፉ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳለች። በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ውስጥ ሰፊ ድርሻ ያለው ቡና ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ ፋይዳ የጀርባ አጥንት ነው። ከሌሎች የግብርና ምርቶች ቡና ከአገር ውስጥ ተጠቃሚዎች አልፎ ለበርካታ ሀገራት በመቅረብም የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት ረገድ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ያለተቀናቃኝ በአውራነት ሊዘልቅ ችሏል። ኢትዮጵያ ቡናን ለመጀመሪያ ጊዜ ለባህር ማዶ ገበያ ያቀረበችው በፈረንጆቹ የዘመን አቆጣጠር 1838 በምጽዋ ወደብ በኩል እንደነበር ታሪክ ይነግረናል። በ19ኛው ክፍለ ዘመን ሁለት የቡና ዓይነቶችን ( ሐረር እና አቢሲኒያ) ለንደንን ጨምሮ ወደ ኒውዮርክ እና ማርሴል ከተሞች በመላክ የኤክስፖርት ንግዱን ተያያዘችው። ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የኤክስፖርት ግብይት በአሁኑ ወቅትም በጥራት እና ብዛት ዕድገት እያሳየ ዘልቋል። ሆኖም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በግብይት ሥርዓቱ ውስጥ የሚፈጠሩ የተለያዩ መሰናክሎች ሳቢያ አርሶ አደሮች የጥረታቸውን ያህል ተጠቃሚ ነበሩ ለማለት ያዳግታል። ከፍተኛ የቡና ምርት መገኛ እንደሆኑ በሚነገርላቸው የተለያዩ አካባቢዎች የኅብረት ሥራ ማኅበራት መመሥረትን ተከት

የኢትዮጵያን የውክልና ሕግ ቢያውቁ ይጠቀማሉ

በኤልያስ ዶጊሶ  ከደቡብ ክልል ፍትህ ቢሮ  እጅግ እየዘመነ በመጣው የዓለማችን የኑሮ ሁኔታ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሕልውና ጥያቄ ሆኗል። በተለይ ሕዝቦች ከከፋ ድህነት ተላቅቀው የተሻለ ሕይወት መምራት እንዲችሉ በኢኮኖሚው መስክ ንቁ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ይጠበቃል፡፡ እንደ ንግድ ያሉ የኢኮኖሚ ዘርፎች ደግሞ አንዳንዴ በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት የተለያየ ስፍራ መገኘትን ይጠይቃል። የሰው ልጅ ደግሞ በተፈጥሮው በጊዜና በቦታ ውሱን ከመሆኑ አንፃር በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት ጥቅሙን በሚመለከቱ ስፍራዎች ሁሉ ተገኝቶ ተግባሩን መከወን አይችልም፡፡ እነዚህ መሰል ጉዳዮችን አስመልክቶ የሰው ልጅ የሚኖረው ብቸኛ አማራጭ እንደራሱ ሆኖ በእርሱ እግር ተተክቶ ጉዳዮቹን ወይም ሥራዎቹን የሚከውንለትን ሰው መወከል ግድ ይሆንበታል፡፡ ሥራዎችን በውክልና ማሰራት አስፈላጊ የሆነው በኢኮኖሚው ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በማህበራዊ የሕይወት መስክም ካለው ጠቀሜታ አኳያ ነው፡፡ በየትኛውም ዘርፍ የሚደረጉ የውክልና ውሎች ማዕቀፋቸው በፍትሐብሔር ሕግ ከአንቀጽ 2179 እስከ 2285 ባሉ ድንጋጌዎች ነው፡፡ በዚሁ ሕግ መሠረት የውክልና ሕግ የእንደራሴነት ሕግ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ሁለቱንም ቃላት መጠቀም በፍቺ ረገድ ልዩነት የላቸውም፡፡ በአማርኛ መዝገበ ቃላት «ወኪል» የሚለውን ቃል እንደዋና ሆኖ የሚሰራ፣ ተጠሪ፣ ኃላፊ፣ ዋናውን ተክቶ እንዲሰራ የተመረጠው ሰው፣ አካል የሚል ሲሆን «ውክልና» ማለትን ደግሞ ለአንድ ሰው ወይም ድርጅት ወኪል፣ ተጠሪ መሆን የሚል ፍቺ ተሰጥቶታል፡፡ በፍ/ሕ/ቁ 2199 መሠረት ደግሞ «ውክልና» ማለትን በሚከተለው መልኩ ይተረጉመዋል፡፡ «ተወካይ የተባለ አንድ ሰው ወካይ ለተባለው ሰው እንደራሴ ሆኖ አንድ ወይም ብዙ ሕጋዊ ሰራዎችን በወካዩ ስም ለማከናወን ግዴታ የሚገባበት ውል ነው።