Posts

ኣዲሱ የሲዳማ ካርታ ሃዋሳ እና ከቅርብ ኣመታት ወዲህ በሃዋሳ ከተማ ስር የተካተቱትን ኣዳዲስ ክፍለ ከተሞችን ኣያካትትም

Image
ኣዲሱ የሲዳማ  ካርታ ያልተካተቱት የሲዳማ ኣካባቢዎች መካከል ሃዋሳ፤ ከቅርብ ኣመታት ወዲህ በሃዋሳ ከተማ ስር የተካተተውን ኣዲሱን ክፍለ ከተማ ኣቤላ ቱላን ጨምሮ ከከተማ ዙሪያ ያሉትን ዳቶ ኦዳሄ እና ሎቄን የመሳሰሉ ቀበሌዎችን ናቸው። የተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑድርጅቶች ለተለያዩ ጉዳዮች ሲዳማን በተመለከተ እየተጠቀሙ ያሉት ኣዲሱ ካርታ ኣዳዲስ ወረዳዎችን ጨምሮ ከላይ የተጠቀሱትን  የሲዳማ ዞን ኣካባቢዎችን በስተቀር ሁሉንም ወረዳዎችን  ያካተተ ሲሆን የሃዋሳን ከተማና  የኣካባቢውን ቀበሌዎች ኣለማከተቱ በቅርቡ በዞኑ ውስጥ ተነስቶ ለነበረው ህዝባዊ ንቅናቄ መንስኤ ከሆነው የማወያያ ጽሁፍ ጋር መያያዝ ኣለመያያዙ ኣልታወቀም።

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ኣመራር ካላ ቤታና ሆጤሳ ሕዝቦች ነጻ የሆነችና የበለጸገች በዘር ያልተከፋፈለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር መተባበር አለባቸው ኣሉ፤ ሲኣን በተለያዩ ጉባኤዎች ላይ የሲዳማን ህዝብ በመወከል ላይ ነው

Image
በእንግሊዝ በተካሄደው ለኣዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ጉባኤ የተገኙት ካላ ቤታና ለተሰብሳቢዎች እንደተናገሩት፤ እኛ ኢትዮጵያውያን በየትኛውም መንገድ ቢሆን ለመተባበር መንገድ ማግኘት አለብን። መለስ ባሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ኢትዮጵያውያንን እየተጠቀመ እንደሆነ ሁሉ እኛ ደግሞ ለመተባበር እርስበርስ መደጋገፍና መተጋገዝ አለብን ያሉት ካላ ቤታና፤   ሕዝቦች ነጻ የሆነችና የበለጸገች በዘር ያልተከፋፈለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር መተባበር አለባቸው” ብለዋል።  የጉባኤን ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦  ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በእንግሊዝ “የንቅናቄያችን የእንግሊዝ አገር ስብሰባ ስኬታማ ውጤቶች” ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ባለፈው ሳምንት መጠናቀቂያ አካባቢ በእንግሊዝ አገር ሪዲንግ ከተማ በአገራችን ስላለው ”የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ የመሬት ነጠቃ እና የፖለቲካ መብቶች ረገጣ” የንቅናቄያችን የእንግሊዝ ንዑስ (chapter) የሁለት ቀን ስብሰባ አካሂዶ ነበር። በተለይ በስብሰባው መጠናቀቂያ ላይ ከዚህ በፊት ጎራ ለይተው እርስበርስ በዘር፣ በዓላማ፣ በአካሄድ፣ በፕሮግራም ወዘተ የነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎችና ቡድኖች - የትግራይ፣ የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የሲዳማ ተወላጆች እንዲሁም ሌሎች የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች፣ ክርስቲያኖች፣ እስላሞች፣ የአንድነት ደጋፊዎች፣ የነጻ አውጪ ግንባሮች፣ የትጥቅ ትግል ደጋፊዎች፣ የሰላማዊ ትግል አራማጆች፣ ወዘተ - በአንድ ቦታ ተገናኝተው ከተወያዩ በኋላ በስብሰባው መጠናቀቂያ ወቅት ሲተቃቀፉ፣ እርስ በርስ በፈገግታ ሲነጋገሩ እንዲሁም የግል መረጃዎቻቸውን ሲለዋወጡ መመልከቱ ብቻ የስብሰባውን ስኬት በግልጽ የሚያሳይ ነበር። ከላይ እንደተገለጸው ንቅናቄያችን ይህንን ስብሰባ ያካሄደበት ዋንኛ ዓላማ

Update on Crisis Caused by the Regime; Shiferaw continues muddling in the internal Affairs of the Sidama ignoring the duty of his regional Presidency!

July 11, 2012 Kukkissa, Our Reporter from Hawassa, Sidama The Sidama people continued their peaceful and nonviolent quest for regional  self administration heroically defying intimidation, harassment, psychological  and physical torture, killings and all kinds and shapes of government  sponsored terrorism targeting low abiding Sidama people who are claiming  nothing other than their Constitutional rights. The Sidama popular resistance  was flared up about seven weeks ago on June 4, 2012 when the regime’s  regional Cadre brought out their illegal and unconstitutional Manifesto on  federalizing Sidama capital Hawassa town that consequently angered Sidama  peoples of all walks of lives from corner to corner; apart from pariah cadres  such as regional president Shiferaw Shuguxe who is currently acting like rabies  infected dogs. Further Reading click here:  Update on Crisis Caused by the Regime

የወንዶ ገነት የደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ሶስት አዳዲስ ፕሮግራሞችን ሊከፍት ነው

Image
ሃዋሳ ሀምሌ 3/2004 በአየር ንብረትና አካባቢ ጥበቃ ላይ በድህረ ምረቃ መርሀ ግብር ሶስት አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች በቅርቡ እንደሚከፍት የወንዶ ገነት የደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ገለጸ፡፡ የኮሌጁ ሃላፊ ዶክተር ጸጋዬ በቀለ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በሁለተኛና በዶክትሬት የትምህርት ደረጃ የሚከፍታቸው ሶስቱ የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ዘላቂ የደን አያያዝና አስተዳደር፣ የላንድ ስኬፕ ማኔጅመንት፣ ክላይሜት ቼንጅ ኤንድ ባዮ ኢነርጂ ዴቬሎፕመንት መርሀ ግብር ናቸው፡፡ በሁለተኛ ድግሪ 30 ተማሪዎችን በዶክትሬት ደረጃ ደግሞ 10 ያህል ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር በአሁኑ ወቅት የስርዓተ ትምህርት ቀረጻ፣ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች የማስፋፋት ስራ ፣ የመምህራን ምደባና ሌሎች ለመማር ማስተማሩ ስራ የሚያስፈልጉ ሌሎችም ቅድመ ዝግጅቶችን እያደረገ በመሆኑ ፕሮግራሞቹ በቅርቡ እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል፡፡ የፕሮግራሞቹ መከፈት የአየር ንብረት፣ የአካካባቢና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማትን በማጎልበትና በማዳበር ሀገራችንን ከድህነት ለማዋጣት የሚደረገውን ጥረት የሚጠናክር በመሆኑ የመንግስት ከፍተኛ ትኩረትና ድጋፍ አንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ ኮሌጁ ነባርና አዳዲስ ፕሮግራሞችን የሚካሄደው በተቀናጀ የምርምርና ጥናት ላይ በመመስረት ህብረተሰቡን በማሳተፍና ችግር ፈቺ መሆናቸውን በማረጋገጥ መሆኑን ገልጸው በተለይ በህብረተሰብ አገልግሎት ዘርፍ ለሴቶች ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ አስታውቀዋል። የደን ልማት የአፈርና ውሃ ጥበቃ፣ የፍራፍሬና አትክልት ልማት ፣ የጥቃቅንና አነስተኛ ስራዎች ላይ በትንሽ ገንዘብ ብዙ ሃብት ማፍራት በሚቻልበትና የግጭት አፈታት ዘዴዎችን ጨምሮ በርካታ ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል፡፡ በደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅነት ለሀገሪ

Participation of Women in rural saving and credit cooperatives: “A case of Shebedino District, Sidama zone, southern Ethiopia”

ABSTRACT I have done this research using qualitative survey method conducted to identify the participation of women in saving and credit cooperatives. This was done in Shebedino district, Sidama zone, South, Nations, Nationalities and people’s regional state, Ethiopia. The data was collected both from primary and secondary sources. Primary data was gathered from the administration of semi structured questionnaires. The questionnaires were focused on collecting the information about participation of women in saving and credit services. A sample size for this research consisted equal proportion of 30 female and male respondents from 3 saving and credit cooperatives. The study also used focus group discussion, interviews, and observation as primary data collection methods. 2 FGD participants (board of directors and non cooperative member women. Questionnaire was filled by key informants from regional, zonal and district level cooperative promoters. Observa