የሲዳማ ፓርቲዎች ህብረት ለነጻነት እና ፍትህ (USPFJ)፤ የራሷ እያረረባት የሰው ታማስላለች!

የሲዳማ ፓርቲዎች ህብረት ለነጻነት እና ፍትህ የሰሞኑ ጋዜጣዊ መግለጫ በኣንባቢያ ዘንድ ክርክር ጫረ

የተባበሩት የሲዳማ ፓርቲዎች ለነጻነት እና ፍትህ በምጻረ_ቃል (USPFJ) ሰሞኑን በኢትዮጵያ ውስጥ በኦሮሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ በኣገሪቱ የጸጥታ ኃይሎች የተወሰደውን የኃይል እርምጃ በመቃወም ጋዜጣዊ መግለጫ ስጥቷል። በመግለጫውም ለበርካታዎች ሞት እና ኣካል ጉዳት ምክንያት የሆነውን የመንግስት እርምጃ ኮንኗል።

ይህንን የድርጅቱን መግለጫ የወራንቻ ኢፎርሜሽን ኔትዎርክ ከጋዳ ድህረገጽ ላይ በማግኘት ለኣንባቢያኑ ያደረሰ ሲሆን፤ የህብረቱን ጋዜጣዊ መግለጫ ተከትሎ የተለያዩ ሰዎች ኣስተያየት በመስጠት ላይ ናቸው።

በርካታ ኣንባቢያን ለወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ በጻፏቸው መልዕክቶች እንዳመለከቱት፤ የተባበሩት የሲዳማ ፓርቲዎች ህብረት ለነጻነት እና ፍትህ፤ በበርካታ ሲዳማውያንን እና የሰብኣዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች የተወገዘውን፦ የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች በቅርቡ በሃዋሳ ከተማ የኣላሙራ እና ታቦር ከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሲዳማ ተወላጅ ተማሪዎች ላይ የወሰዱትን የኃይል ጥቃት ካለማውገዙ በላይ በጥቃቱ ልጆቻቸው ለተጎዱባቸው ቤተሰቦች ኣጋርነቱን ኣለመግለጹን እንዳዛዘናቸው ገልጸዋል።

ከኣስተያየት ስጪዎቹ መሃከል፦ ስሙን T H በማለት የጠራው እና የዩቨርሲቲ መምህር መሆኑን የገለጸው ኣስተያየት ሲጪ እንዳለው፤ ህብረቱ ምንም እንኳን እታገልለታለው ከሚለው ህዝብ ጋር የግንባር ለግንባር ግንኙነት የሌለው ብሆንም ባለፉት ኣመታት በሲዳማ ውስጥ ያለውን የፖለቲካ እና ስብኣዊ መብት ጥስቶችን በማጋለጥ ከፍተኛ ሚና መጫወቱን ኣስተውሰዋል።

ኣክለውም ህብረቱ በቅርቡ በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ በመንግስት የተወሰደውን የኃይል እርምጃ ማውገዙ ምንም ስህተት እንደሌለው ገልጸው፤ የህብረቱ ድርጊት በባህል ከሲዳማ ህዝብ ጋር ኣንድ ለሆነው የኦሮሞ ህዝብ መብት መከበር ያለውን ድጋፍ እና ኣጋሪነት ያሳያል ብለዋል።

ኣያይዘውም የህብረቱ መግለጫ የሲዳማ ህዝብ እና የኦሮሞ ህዝብ በጋራ በተለያዩ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮቻቸው ላይ እንድሰሩ መንገድ ይከፍታል በማለት ኣስተያየታቸውን ስጥተዋል።

ካላ ቃዋቶ ቤላሞ የተባሉት ሌላኛው ኣስተያየት ሲጪ በበኩላቸው፤ ህብረቱ በኣሮሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ የተፈጸመውን ግፍ መቃዎሙ ትክክል ሆኖ ሳለ፤ በተመሳሳይ መልኩ በሲዳማ ተማሪዎች ላይ የተፈጸመውን ግፍ ተቃዉሞ መግለጫ ኣለመስጠቱ ኣሳዛኝ ነው ብለዋል።

እኝሁ ኣስተያየት ሲጪ እንዳሉት፦ የሃዋሳ ከተማ ኣላሙራ እና ታቦር ትምህርት ቤት ተማሪዎች ያነሷቸው የመብት ጥያቄዎች ማንኛውም ለሲዳማ ህዝብ መብት እታገላለው የምል ኣካል በሙሉ ሊያነሳው የሚገባ ኣንገብጋብ የመብት ጥያቄ በመሆኑ ህብረቱ ለተማሪዎቹ ያለውን ድጋፍ በኣደባባይ መግለጽ ይገባው ነበር በማለት ኣስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

የካላ ቃዋቶች ኣስተያየት የተጋሩ ሌላኛው ኣስተያየት ሰጪ እንደጻፉት፦ የተባበሩት የሲዳማ ፓርቲዎች ህብረት ለነጻነት እና ፍትህ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ በማህበራዊ ገጾች ላይ የሚጽፋቸው ጽሁፎች በብዛት የኦሮሞ ህዝብ የተመለከቱ ናቸው ብለዋል።

ኣክለውም የራሷ እያረረባት የሰው ታማስላለች እንደምባለው በሲዳማ ፖለቲካዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ላይ ትኩረት ስጥቶ መስራት እያለበት በሌላ ኣጄንዳ ላይ ትኩረት መስጠቱ በሲዳማ ህዝብ ዘንድ ያለው ተቀባይነት ያሳጣዋል ብለዋል።

ክቡራን ኣንባቢያን በጉዳዩ ላይ ያላችሁን ኣስተያየት በሚከተለው ኣድራሻ ይላኩልን:
Worancha Information Network
e-mail: nomonanoto@gmail.com 
እኛም ከሰፊው የሲዳማ ህዝብ ጋር እንጋራዋለን።


Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር