Deadly Protests in Ethiopia Over Plans to Expand Capital — At Least 17 Killed

Photo: Addis Ababa University Students Urge John Kerry to condemn the police violence against fellow students in Ambo -- a town located in the Oromia region of Ethiopia. (Picture: Twitter.com May 1, 2014 ) - See more at: http://www.tadias.com/05/02/2014/deadly-protests-in-ambo-ethiopia-over-plans-to-expand-capital-17-killed/#sthash.R2GfovTw.dpuf

ከአዲስ አበባና የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ ማስተር ፕላን ጋር በተገናኘ ተማሪዎች ተቃውሞ አሰሙ

-የኦሮሚያ ክልል የታሰረም ሆነ የተደበደበ ተማሪ የለም አለ
በአዲስ አበባና በዙሪያዋ ያሉ የኦሮሚያ ክልል ልዩ ዞንን በአንድ የማስተር ፕላን ማቀናጀት ምክንያት፣ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች በሚገኝ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት የሚማሩ የኦሮሚያ ተማሪዎች ተቃውሞ ማድረጋቸውን ምንጮች ገለጹ፡፡ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ስለ ተማሪዎቹ ተቃውሞ በግልጽ ያለው ነገር ባይኖርም፣ በፀጥታ ኃይሎች ድብደባና እስራት ተፈጽሞባቸዋል መባሉን ግን አስተባብሏል፡፡
ለአዲስ አበባና ለኦሮሚያ ልዩ ዞኖች የተዘጋጀው የተቀናጀ ማስተር ፕላን ካለፉት ጥቂት ሳምንታት ጀምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የኦሮሚያ ክልል አመራሮች ሲወያዩበት መቆየታቸውን፣ ይህንን ተከትሎ ሕገ መንግሥታዊ ጥያቄዎች ማስነሳቱንም ጨምሮ መዘገባችን ይታወሳል፡፡ 
ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ግን የኦሮሞ ተወላጆች ናቸው በተባሉ ተማሪዎች በአገሪቱ በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ በተለይም በጂማ፣ በአምቦ፣ በወለጋና በሀረማያ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ተማሪዎች አዲሱ የተቀናጀ ማስተር ፕላን የኦሮሚያን ጥቅም ‹‹ለማሳጣት እንጂ ለክልሉ ታስቦ አይደለም›› በማለት፣ መጠነኛ ተቃውሞ ማድረጋቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ 
በተለይ በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ወደ ከተማ በመውጣት በአደባባይ የተቃወሙ ሲሆን፣ አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል ብቻ መሆኗን የሚያሳዩ መፈክሮችንም አሰምተዋል፡፡ እንደዚሁም በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ሚያዝያ 18 ቀን 2006 ዓ.ም. ለተቃውሞ በወጡ ተማሪዎች ላይ ፖሊስ ተማሪዎቹን ሲበትን የተወሰኑ ተማሪዎች ከግቢው በመውጣት መሸሻቸውን ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ነገር ግን በአንዳንድ ድረ ገጾችና ማኅበራዊ ሚዲያዎች የፀጥታ ኃይሎች የተማሪዎችን ሰላማዊ ተቃውሞ በጉልበት ማፈናቸውን፣ እስራትና ድብደባ በተማሪዎች ላይ መፈጸሙን እየዘገቡ ይገኛሉ፡፡
በተማሪዎች ተፈጸመ የተባለውን ድብደባና እስራት አስመልክቶ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ አጭር ምላሽ የሰጡት የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አብዱላዚዝ መሐመድ፣ ‹‹አንድም የታሰረም ሆነ የተደበደበ ተማሪ የለም፣ መረጃውም አልደረሰንም፤›› ብለዋል፡፡
መንግሥት በበኩሉ የአዲስ አበባና የፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የጋራ የልማት መሪ ዕቅድ የእርስ በርስ ትስስር ያላቸውን ከተሞች የልማት ጥያቄ ለመመለስ ያለመ ነው ሲል አስታውቋል፡፡ ‹‹… የጋራ የልማት መሪ ዕቅዱ ሕገ መንግሥቱ ለብሔር ብሔረሰቦች ያረጋገጠውን በጋራና በፍትሐዊነት የመልማት መብት የሚያረጋግጥ እንጂ ከወሰንና ከመሬት ጋር የሚያያዘው አንዳችም መሠረት የለውም፤›› በማለት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊሲ ጉዳዮች አማካሪ የሆኑትና የቀድሞ የአዲስ አበባ ከንቲባ አቶ ኩማ ደመቅሳ ለኢቲቪ ገልጸዋል፡፡ 
በተጨማሪም አቶ ኩማ ጉዳዩን አጀንዳ በማድረግ ሕዝቡን የሚያሳስቱ አሉባልታዎች ተጨባጭነት እንደሌላቸውም ጨምረው ገልጸዋል፡፡ አቶ አብዱላዚዝ በበኩላቸው፣ የጋራ ልማት መሪ ዕቅዱ የልማት ጥያቄን የሚመልስ እንጂ ከአስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር የሚገናኝ እንዳልሆነ አስረድተዋል፡፡     
VOA News
May 01, 2014
Witnesses say Ethiopian police have killed at least 17 protesters during demonstrations in Ethiopia’s Oromia region against plans to annex territory to expand the capital, Addis Ababa.
Authorities put the protest-related death toll at 11 and have not said how the demonstrators were killed. The main opposition party says 17 people were killed while witnesses and residents say the death toll is much higher.
Residents say that an elite government security force opened fire on protesters at three university campuses.
The demonstrations erupted last week against plans by the Ethiopian government to incorporate part of Oromia into the capital. Oromia is Ethiopia’s largest region and Oromos are the country’s largest ethnic group.
Oromos say the government wants to weaken their political power. They say expanding the capital threatens the local language, which is not taught in Addis Ababa schools.
Ethiopian officials say the master plan for expansion was publicized long ago and would bring city services to remote areas.
They accuse those they call “anti-peace forces” of trying to destroy Ethiopia’s ethnic harmony.
- See more at: http://www.tadias.com/05/02/2014/deadly-protests-in-ambo-ethiopia-over-plans-to-expand-capital-17-killed/#sthash.R2GfovTw.dpuf

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር