በመኸር እርሻ ሥራ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደገ እየሰሩ መሆናቸውን በሲዳማ ዞን የጐርቼ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለፁ፡፡
በወረዳው በ2ዐዐ5 እና በ2ዐዐ6 ዓ/ም የመኸር እርሻ ከ3 ሺህ 57ዐ ሄክታር በላይ መሬት በዋና ዋና ሰብሎች ዘር ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡፡
አርሶ አደር አመሎ ኪቦ አና አርሶ አደር ቀጤ ወጀቦ በወረዳው የሐርቤ ሚቀና ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ የመኸር እርሻ ሥራን ውጤታማ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ገልፀው በተለያዩ ጊዜያት ባገኙት የክህሎት ሥልጠና በመጠቀም ጥምርታቸውን በጠበቀ መልኩ በመዝራት ላይ እንዳሉ ተናግረዋል፡፡
አርሶ አደር አመሎ ኪቦ አና አርሶ አደር ቀጤ ወጀቦ በወረዳው የሐርቤ ሚቀና ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ የመኸር እርሻ ሥራን ውጤታማ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ገልፀው በተለያዩ ጊዜያት ባገኙት የክህሎት ሥልጠና በመጠቀም ጥምርታቸውን በጠበቀ መልኩ በመዝራት ላይ እንዳሉ ተናግረዋል፡፡
የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ስጦታው ከንባታ በበኩላቸው በ2ዐዐ5 እና በ2ዐዐ6 ዓ/ም የመኸር እርሻ ከ3 ሺህ 57ዐ ሄክታር በላይ መሬት በዋና ዋና የሰብል ዘሮች ለመሸፈን የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝና እስከ አሁንም 3 መቶ 36 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈናቸውን ገልፀዋል፡፡
በመኸር እርሻ በዘር ከሚሸፈን ማሳ አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል ሲል የዘገበው የወረዳው የመንግሰት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው፡፡
ምንጭ፦http://www.smm.gov.et/_Text/13NehTextN805.html
በመኸር እርሻ በዘር ከሚሸፈን ማሳ አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል ሲል የዘገበው የወረዳው የመንግሰት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው፡፡
ምንጭ፦http://www.smm.gov.et/_Text/13NehTextN805.html
Comments
Post a Comment