በ40/60 ምዝገባ ለመመዝገብ ለምሹ የሲዳማ ዳይስፖራ

በ40/60 ቤቶች ግንባታ ፕሮግራም ምዝገባ ሒደት በመረጃ ፍሰት መደነቃቀፍ ግራ መጋባት ውስጥ የነበሩ የዳያስፖራ አባላት በሳምንቱ መጨረሻ መረጃቸውን እያስተካከሉ ምዝገባ መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ፡
በሌላ በኩልም ባንኩ ከ500 ሺሕ እስከ 800 ሺሕ የሚደርሱ ሰዎች በዚህ የ40/60 ፕሮግራም ይመዘገባሉ ብሎ ቅድሚያ ግምት ቢሰጥም፣ ባለፈው ዓርብ ምሽት ማተሚያ ቤት እስከገባንበት ሰዓት ምዝገባ ያካሄዱ ሰዎች ቁጥር  ከታሰበው እጅግ ያነሰ (81,257) መሆኑ ታውቋል፡፡ 
የ40/60 ቤቶች ምዝገባ ባለፈው ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ 116 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎችና መገናኛ አካባቢ ከአምቼ ፊት ለፊት በሚገኘው የአዲስ አበባ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ተጀምሯል፡፡
ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ውስጥ የሚካሄደው ምዝገባ በውጭ አገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን (ዳያስፖራ) የተመደበ ነው፡፡ በዚህ የምዝገባ ጣቢያ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በግንባር ቀርበው ወይም በወኪላቸው አማካይነት ምዝገባ ያካሂዳሉ፡፡
ነገር ግን በተለይ በውጭ አገር ሆነው በግንባር መቅረብ ያልቻሉ ኢትዮጵያውያን ከሌላ ምንጭ የሚሰሙት መረጃና ከወኪላቸው የሚሰሙት መረጃ እየተጣረሰባቸው ግራ ተጋብተው መሰንበታቸውን የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡
ምዝገባው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ቀናት የምዝገባ ፍሰቱ መደነቃቀፉንና በሳምንቱ መጨረሻ ፍሰቱ እየተስተካከለ መምጣቱን፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ባንኩ በዳያስፖራዎች ምዝገባ ጣቢያ ገለጻ በመስጠት ያለውን የመረጃ ክፍተት በመሙላት ላይ ሲሆን፣ እስከ ዓርብ ምሽት ድረስ በአጠቃላይ ከተመዘገቡት ውስጥ ሦስት ሺሕ የሚጠጉት ዳያስፖራዎች መሆናቸው ታውቋል፡፡
በ40/60 ቤቶች ፕሮግራም የቀረቡት ቤቶች ባለአንድ መኝታ 55 ካሬ ሜትር፣ ባለሁለት መኝታ 75 ካሬ ሜትርና ባለሦስት መኝታ ቤት 100 ካሬ ሜትር ስፋት አላቸው፡፡ የባለአንድ ክፍል የመሸጫ ዋጋ 162,645 ብር ሲሆን፣ የዚህ 40 በመቶ 61,960 ብር ነው፡፡ የባለሁለት ክፍል 250 ሺሕ ብር ሲሆን፣ 40 በመቶው 94,470 ብር ነው፡፡  ባለሦስት ክፍል ደግሞ 386,400 ብር ሲሆን፣ 40 በመቶው 147,200 ብር ነው፡፡ ተመዝጋቢዎች ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ይህንን 40 በመቶ ቆጥበው የቤት ባለቤት መሆን ይችላሉ፡፡ ነገር ግን በቅድሚያ ሙሉ በሙሉ ክፍያ የሚፈጽሙት ቅድሚያ ዕድል ያገኛሉ መባሉ ይታወቃል፡፡
ይህ ዋጋ እንደየወቅቱ የኮንስትራክሽን ዋጋ እንደሚቀያየር ተገልጿል፡፡ በአሁኑ ወቅት በተለይ እስከ ዓርብ ድረስ አብዛኛዎቹ ተመዝጋቢዎች ባለሁለትና ባለሦስት መኝታ ቤት ለማግኘት ምዝገባ ያካሄዱ ሲሆን፣ ከእነዚህ ተመዝጋቢዎች ውስጥ የተወሰኑት ሙሉ ክፍያና 40 በመቶውን ከፍለዋል፡፡
መንግሥት በድርሻ ደረጃ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ባለአንድ መኝታ፣ በመቀጠል ባለሁለት መኝታና፣ በሦስተኛ ደረጃ ባለሦስት መኝታ ቤቶችን በየቅደም ተከተላቸው ለመገንባት አቅዶ ነበር፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት እየወጡ ባሉ መረጃዎች በተመዝጋቢው ፍላጎት ላይ የተመሠረተ የቤት ግንባታ ማካሄድ ስለሚያስፈልግ የቤቶቹ ዲዛይን ሊከለስ እንደሚችል እየተነገረ ነው፡፡  

በ40/60 ምዝገባ ግራ ተጋብተው የነበሩት ዳያስፖራዎች መመዝገብ ጀመሩ
በውድነህ ዘነበ
በ40/60 ቤቶች ግንባታ ፕሮግራም ምዝገባ ሒደት በመረጃ ፍሰት መደነቃቀፍ ግራ መጋባት ውስጥ የነበሩ የዳያስፖራ አባላት በሳምንቱ መጨረሻ መረጃቸውን እያስተካከሉ ምዝገባ መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ፡፡
በሌላ በኩልም ባንኩ ከ500 ሺሕ እስከ 800 ሺሕ የሚደርሱ ሰዎች በዚህ የ40/60 ፕሮግራም ይመዘገባሉ ብሎ ቅድሚያ ግምት ቢሰጥም፣ ባለፈው ዓርብ ምሽት ማተሚያ ቤት እስከገባንበት ሰዓት ምዝገባ ያካሄዱ ሰዎች ቁጥር  ከታሰበው እጅግ ያነሰ (81,257) መሆኑ ታውቋል፡፡ 
የ40/60 ቤቶች ምዝገባ ባለፈው ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ 116 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎችና መገናኛ አካባቢ ከአምቼ ፊት ለፊት በሚገኘው የአዲስ አበባ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ተጀምሯል፡፡
ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ውስጥ የሚካሄደው ምዝገባ በውጭ አገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን (ዳያስፖራ) የተመደበ ነው፡፡ በዚህ የምዝገባ ጣቢያ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በግንባር ቀርበው ወይም በወኪላቸው አማካይነት ምዝገባ ያካሂዳሉ፡፡
ነገር ግን በተለይ በውጭ አገር ሆነው በግንባር መቅረብ ያልቻሉ ኢትዮጵያውያን ከሌላ ምንጭ የሚሰሙት መረጃና ከወኪላቸው የሚሰሙት መረጃ እየተጣረሰባቸው ግራ ተጋብተው መሰንበታቸውን የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡
ምዝገባው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ቀናት የምዝገባ ፍሰቱ መደነቃቀፉንና በሳምንቱ መጨረሻ ፍሰቱ እየተስተካከለ መምጣቱን፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ባንኩ በዳያስፖራዎች ምዝገባ ጣቢያ ገለጻ በመስጠት ያለውን የመረጃ ክፍተት በመሙላት ላይ ሲሆን፣ እስከ ዓርብ ምሽት ድረስ በአጠቃላይ ከተመዘገቡት ውስጥ ሦስት ሺሕ የሚጠጉት ዳያስፖራዎች መሆናቸው ታውቋል፡፡
በ40/60 ቤቶች ፕሮግራም የቀረቡት ቤቶች ባለአንድ መኝታ 55 ካሬ ሜትር፣ ባለሁለት መኝታ 75 ካሬ ሜትርና ባለሦስት መኝታ ቤት 100 ካሬ ሜትር ስፋት አላቸው፡፡ የባለአንድ ክፍል የመሸጫ ዋጋ 162,645 ብር ሲሆን፣ የዚህ 40 በመቶ 61,960 ብር ነው፡፡ የባለሁለት ክፍል 250 ሺሕ ብር ሲሆን፣ 40 በመቶው 94,470 ብር ነው፡፡  ባለሦስት ክፍል ደግሞ 386,400 ብር ሲሆን፣ 40 በመቶው 147,200 ብር ነው፡፡ ተመዝጋቢዎች ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ይህንን 40 በመቶ ቆጥበው የቤት ባለቤት መሆን ይችላሉ፡፡ ነገር ግን በቅድሚያ ሙሉ በሙሉ ክፍያ የሚፈጽሙት ቅድሚያ ዕድል ያገኛሉ መባሉ ይታወቃል፡፡
ይህ ዋጋ እንደየወቅቱ የኮንስትራክሽን ዋጋ እንደሚቀያየር ተገልጿል፡፡ በአሁኑ ወቅት በተለይ እስከ ዓርብ ድረስ አብዛኛዎቹ ተመዝጋቢዎች ባለሁለትና ባለሦስት መኝታ ቤት ለማግኘት ምዝገባ ያካሄዱ ሲሆን፣ ከእነዚህ ተመዝጋቢዎች ውስጥ የተወሰኑት ሙሉ ክፍያና 40 በመቶውን ከፍለዋል፡፡
መንግሥት በድርሻ ደረጃ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ባለአንድ መኝታ፣ በመቀጠል ባለሁለት መኝታና፣ በሦስተኛ ደረጃ ባለሦስት መኝታ ቤቶችን በየቅደም ተከተላቸው ለመገንባት አቅዶ ነበር፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት እየወጡ ባሉ መረጃዎች በተመዝጋቢው ፍላጎት ላይ የተመሠረተ የቤት ግንባታ ማካሄድ ስለሚያስፈልግ የቤቶቹ ዲዛይን ሊከለስ እንደሚችል እየተነገረ ነው፡፡  

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር