አመራሩ የኪራይ ሰብሳቢነትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከምንጩ ለይቶ መታገል ይገበዋል-የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር

አዋሳ ግንቦት 01/2005 የኪራይ ስብሳቢነትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከምንጩ በመለየት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አመራሩ መረባረብ እንዳለበት የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አሳሰቡ፡፡ በክልል የሚገኙ ከአንድ ሺህ በላይ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በከተሞች የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የሰራዊት ግንባታ አፈፃፀም ያለበት ሁኔታና ቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ ላይ ለሁለት ቀን ያካሄዱት ውይይት ትናንት ማምሻው ተጠናቋል፡፡ ርዕሰ መስተዳደሩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት በከተሞች የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አንድ በአንድ ለይቶ በማውጣት ለህብረተሰቡ ተገቢውን ምላሽ መስጠት የአመራሩ ቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ በየከተሞች ጎልቶ እየታየ ለመጣው የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በዋናነት ተጠያቂው አመራሩ በመሆኑ እነዚህን ችግሮች ሌት ከቀን በመረባረብ መፍታት እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡ የከተማ ነዋሪዎች ለልማት ስራዎች ያላቸውን ፍላጎትና መነሳሳት አደራጅተውና አቀናጅቶ በመምራት፣ ይህን የልማት አቅም የመጠቀም ውስንነት በአመራሩ ዘንድ በሰፊው የሚታዩ ችግሮች ስለሆነ በፍጥነት ተፈቶ ወደ ስራ መገባት አለበት ብለዋል፡፡ በከተሞች ከዕቅድ ዝግጅት ጀምሮ ያሉ ስራዎችን አንድ በአንድ የመፈተሽ፣ በልማት ሰራዊት የሚሰሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን በየቀኑ የመከታተል፣ እንዲሁም ለስራው ስኬት የሚያግዙ ግብአቶችን በወቅቱ የማቅረብ ጉዳይ ልዩ ትኩረት ተሰቶ ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በከተሞች የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ዓለማ ለማሳካት የዜጎች፣ የባለሙያዎች፣ የባላሃብቶችና የአመራሮች መሰረታዊ የአስተሳሰብ ለውጥ የሚጠይቅ ቢሆንም አመራሩ የመሪነት ሚናውን በተገቢው መንገድ ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ ጠንካራ የልማት ሰራዊት በከተሞች የመንገባት፣ የህብረተሰብን የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና ሌሎች ጥያቄዎችን በንቃት የሚመልስ አመራር መገንባት እንዲሁም ልማታዊ አስተሳሰብ ያለውን ህብረተሰብ በከተሞች የመፍጠር ጉዳይ ቁልፍ ተግባር ሆኖ ሊቀጥል ይገበዋል ብለዋል፡፡ በከተሞች የሚካሄደው የልማትም ሆነ የመልካም አስተዳደር ስራዎች ባለቤት ነዋሪው በመሆኑ የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና ተግባር በልማታዊ አስተሳሰብና ተግባር ለመተካት በሚደረገው ርብርብ ህብረተሰቡ በንቃት እንዲሳተፉ የማድረግ ስራዎች ትኩረት ሊሰጠው ይገበዋል ብለዋል፡፡
Read more:http://www.ena.gov.et/story.aspx?ID=7779

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር