ሲዳማን ጨምሮ የሸማቾችን ቅሬታ የሚሰብሰብ የነጻ የስልክ መስመር በስራ ላይ ዋለ


የንግድ አሰራርና የሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን የሸማቹን ህብረተሰብ ቅሬታ ለመሰብሰብ የሚያስችል አዲስ የነጻ የስልክ መስመር ጥሪ በስራ ላይ ማዋሉን አስታወቀ፡፡
የባለስልጣኑ የሸማቾች ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ ግርማ አለማር መጋቢት 26/2005 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ የሸማቹን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ የሚረዳ 8478 የመስመር ቁጥር  ያለው ነጻ ጥሪ ከመጋቢት 26/2005 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ላይ ውሏል ብለዋል፡፡ 
ይህም በአገሪቱ በማንኛውም አካባቢ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን የንግድ ስርዓቱ በህግ አግባበ ለመዳኘት የሚሰራውን ስራ ለማጠናከር እንደሚረዳ አብራርተዋል፡፡
መስመሩ በአንድ ጊዜ አራት ጥሪዎችን መቀበል የሚያስችል ሲሆን ህብረተሰቡም በነጻ የስልክ መስመሩ በመጠቀም በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚደርስባቸውን የመብት ጥሰትና የጸረ ንግድ ውድድር ተግባራት ሲፈጸም ጥቆማ ለማድረስ እንደሚረዳ ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም ሸማቹን ለጤና መታወክ የሚዳርጉ ምርቶች በገበያ ሲያጋጥማቸው በነጻ የስልክ መስመሩ ለባለስልጣኑ ቢጠቀሙ ተገቢውን ምላሽ ያገኛሉ ብለዋል፡፡

ምንጭ ፋና ብሮድካስት

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር