የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ጉባኤ ተጨማሪ በጀትና ሹመት በማፅደቅ ተጠናቀቀ

የካቲት 28/2005 የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አባላት በከተማው የተጀመሩ የልማት፣ መልካም አስተዳደርና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ስኬት በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ስራዎችን ለማጠናቀቅ ርብርብ ማድረግ እንዳለባቸው ተገለፀ። የምክር ቤቱ ጉባኤ የአንድ መምሪያ ኃላፊ ሹመትና ተጨማሪ በጀት በማጽደቅ ተጠናቋል። ጉባኤው ትናንት ማምሻውን ሲጠናቀቅ የምክር ቤቱ ዋና አፈጉባኤ አቶ ደምሴ ዳንጊሶ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት በከተማው የተገኘውን ዕድገት ለማስቀጠል የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት አባላት ህዝብ የጣለባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት በቁርጠኝነት መነሳት አለባቸው። የታየውን ውስንነት በማስወገድና የተከናወኑ መልካም ስራዎችን በማጠናከር ለበጀት ዓመቱ የተያዙ ዕቅዶችን በማጠናቀቅ በከተማው የተጀመሩ የልማት መልካም አስተዳደርና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ በተጠናከረ ሁኔታ መከናወን እንዳለባቸው ገልጸዋል። ጉባኤው በትናንት ውሎው በከተማው ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሰፍ የቀረበውን የ2005 የበጀት ዓመት የስድስት ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በመገምገም በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። ጉባኤው በተለያየ ምክንያት ወደ ሌላ ሴክተር መስሪያ ቤት በተዛወሩ መምሪያ ኃላፊ ምትክ አዲስ መምሪያ ኃላፊ ሾሟል።በዚሁ መሰረት ወይዘሮ ገነት ገረመውን የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ በማድረግ ሾሟል፡፡ ጉባኤው በሀዋሳ ከተማ ለሚከናወኑ የልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች ማስፈጸሚያ የሚውል 57 ሚሊዮን 682 ሺህ 599 ብር ተጨማሪ በጀት በማጽደቅ ተጠናቋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ባለፈው ሐምሌ ለ2005 በጀት ዓመት በከተማው ለሚከናወኑ ተግባራት ማስፈጸሚያ 921 ሚሊዮን 958 ሺህ 298 ብር በጀት ማጽደቁ የሚታወስ ነው።http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=6132&K=1

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር