የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫ እየተካሄደ ነው።
ሰሞኑን በሃዋሳ ከተማ ጉባኤውን ሲያካሂድ የሰነበተው ደኢህዴን ከረፋድ ጀምሮ የማዕከላዊ ኮሚቴ እና የስራ አስፈጻሚ አባላትን ምርጫ እያካሄደ ይገኛል።
ለድርጅቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫ 70 ዕጩዎች የተጠቆሙ ሲሆን ፥ ክአንዚህ ውስጥ 65ቱን በመምረጥ ከፍተኛ ድምጽ ያገኙ 9 ዕጩዎች ለኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እንዲሁም 15 ዕጩዎች ደግሞ ለደኢህዴን ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴነት ይመረጣሉ።
በጉባኤው እጩ ሆነው ከቀረቡት መካከል አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ፣ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ፣ ዶክተር ካሱ ኢላላ ፣ አቶ አለማየሁ አሰፋ ፣ አቶ ታገሰ ጫፎ ፣ አቶ ሳኒ ረዲ እና ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ይገኙበታል።
ምርጫው በአሁኑ ሰአት እየተካሄደ ሲሆን እንደተጠናቀቀም ውጤቱ ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
Comments
Post a Comment