9ኛው የኢህአዴግ ጉባዔ ተጠናቀቀ


ከመጋቢት 14 እስከ 17/2005 ዓ.ም በባህርዳር ሲካሄድ የሰነበተው ኢህአዴግ 9ኛው ጉባኤ ዛሬ መጋቢት 17/2005 ተጠናቀቀ፡፡
ጉባኤው የተጠናቀቀው የአቋም መግለጫ በማውጣትና የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ፣ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ደመቀ መኮንን በመምረጥ ነው ፡፡
9ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ ሲጠናቀቅ የአቋም መግለጫ አውጥቷል፡፡ የሚከተሉት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
Ø   በተሃድሶ እንቅስቃሴና በሂደት የጎለበተው ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ መስመራችን በትክክለኛ መንገድ እየሄደ ነው፡፡
Øየልማት ሃይሎችን በተደራጀ መልኩ በመምራት እስከአሁን አሟጠን ያልተጠቀምናቸው እድሎች በመጠቀም ህዳሴያችን  ለማሳካት እንረባረባለን፡፡
Ø  በልማት ሰራዊት ግንባታ የሚታዩት ጉድለቶች በመፍታት የግብርና ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የዋጋ ግሽበትን በመቀነስና የህዝባችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንሰራለን፡፡
Ø  በአነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት ልማታዊ ሰራዊት በተጠናከረ መልኩ በመገንባት የኢንዱስትሪ እድገት ለማረጋገጥ ከወትሮው በላይ በቁርጠኝነት እንሰራለን፡፡
Ø  በዋና ዋና የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የሚታይ  የማስፈጸም አቅምና የገንዘብ አቅርቦት ችግር ለመፍታት እንረባረባለን፡፡
Ø  በትምህርትና በጤና ዘርፍ የሚታየውን የጥራትና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር በመቅረፍ እየተመዘገበ ያለውን ስኬት አጠናክረን እንቀጥልበታለን፡፡
Ø  የኪራይ ሰብሳቢነት ምንጮች በማድረቅና ልማታዊ ሲቪል ሰርቪስ በመፍጠር ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንሰራለን፡፡
Ø  በገጠርና በከተሞች የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ግድፈቶች ለመቅረፍ ከህዝቡ ጋር ተቀናጅተን እንሰራለን፡፡
Ø የአጋር ድርጅቶች የማስፈጸም አቅምን ለማጎልበትና የክልላቸውን ህብረተሰብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት እንዲፈጽሙ ድጋፍ እናደርጋለን ፡፡
Ø  ህገ መንግስታችን መርሆዎች የሚጋጩ የአክራሪነት አስተሳሰቦች ከመላው ህዝባችንጋር በመሆን እንታገለዋለን፡፡
Ø  ህጋዊና ሰላማዊ መንገድን ተከትለው ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተባብረን እንሰራለን፡፡
Ø  የመሪያችን የመለስ ዜናዊ መርሆዎችና አስተምርሆዎች መላው ህዝብ እንዲያውቃቸውና እንዲጠቀምባቸው ለማድረግ በትጋት እንሰራለን፡፡

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር