በሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ የሴታሞና አካባቢው መሠታዊ ሁለ ገብ የገበሬዎች አገልግሎት ህብረት..፡፡

በሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ የሴታሞና አካባቢው መሠታዊ ሁለ ገብ የገበሬዎች አገልግሎት ህብረት ስራ ማህበር ግማሽ ሚሊዮን በሚበልጥ የገንዘብ ድጋፍ በሁለት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሁለት የመማሪያ ክፍሎችን እያስገነባ መሆኑን አስታወቀ፡፡
የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ ቢፋቶ ብሬ አንደገለፁት መንግስት የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋፋት እያደረገ ያለው ጥረት ስኬታማ እንዲሆን ማህበራትም የራሳቸውን ድርሻ ማበርከት ይኖባቸዋል፡፡
በዚህ መነሻ ማህበሩ ሴታሞና ሾእቾ በተባሉ ሁለት ቀበሌያት የሚገኙ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለማስፋፋት በተያዘው እቅድ መሠረት ለእያንዳንዳቸው ደረጃቸውን የጠበቁ አንዳንድ ብሎክ እያስገነባ ይገኛል ብለዋል፡፡
ትምህርት ቤቶቹ በተጀመረው የትምህርት ዘመን አገልግሎት እንዲሰጡ ግንባታቸውን እየተፋጠነ መሆኑን የተናገሩት ሊመቀንበሩ ከ2ዐ ሺህ በላይ ብር ከማህበሩ ወጪ በማድረግ በ4 የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ 1 ሺህ 354 ተማሪዎች የትምህር ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉንም ጠቁመዋል፡፡
የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት እንደዘገበው፡:
http://www.smm.gov.et/_Text/26TikTextN805.html

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር