የህፃናት መብቶችን በተመለከተ ከጊዜ ወደ ጊዜ የህብረተሰቡ ግንዛቤ እያደገ መምጣቱን በኢትዮጵያ ሠብአዊ መብት ኮሚሽን ሀዋሣ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ጽህፈት ቤቱ 7ኛውን የአለም ህፃናት ቀን ከትምህርት ቤቶች ጋር አክብbል፡፡
የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ አስተባባሪ አቶ አብርሃ አታሮ እንዳሉት ትምህርት ቤቶች ሰብአዊ መብትን በተመለከተ ህፃናት ተኮትኩተው የሚያድጉበት በመሆኑ የኮሚሽኑን አላማ ለማሳካት ትልቅ ፋይዳ አላቸው፡፡
መጪው ትውልድ ሰብአዊ መብቶችን ለማክበርና ለማስከበር የሚያስችለውን ስንቅ ከትምህርት ቤቶች ይቀስማል ብለዋል ፡፡
በሀገራችን ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ የሚከበረው የዓለም ህፃናት ቀን “ሁሉም ህፃናት ሰብአዊ መብቶችን በማከበር፣ በማስከበርና ሌሎችንም በማስገንዘብ ትምህርት ቤቶች ትልቅ ሚና አላቸው” የሚል መርህ አላው፡፡
በበአሉ አለም አቀፍ የህፃናት መብቶች ኮንቬንሽንን፣ የአፍሪካ ህፃናት ሰብአዊ መብትንና የኢትዮጵያ መንግስት ለሠብአዊ መብቶች የሠጠውን ትኩረት የሚዳስስ ጽሑፍ ቀርቧል፡፡
የበአሉ ተሳታፊ ህፃናቶች የተለያዩ ጭውውቶችንና ሥነ ጽሑፎችን አቅርበዋል፡፡
ትምህርት ቤቶች በሥነ ምግባር የታነፀ የሞራል እሴት ያለው፣ የነቃና ህግ አስከባሪ ዜጋ ለመፍጠር የሚያደርጉትን ጥረት  ህብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት እንዲደግፉ ጥሪ ቀርቧል ፡፡ ባለደረባችን ደስታ ወ/ሰንበት እንደዘገበው፡፡http://www.smm.gov.et/_Text/11HidTextN305.html

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር