የህፃናት መብቶችን በተመለከተ ከጊዜ ወደ ጊዜ የህብረተሰቡ ግንዛቤ እያደገ መምጣቱን በኢትዮጵያ ሠብአዊ መብት ኮሚሽን ሀዋሣ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
ጽህፈት ቤቱ 7ኛውን የአለም ህፃናት ቀን ከትምህርት ቤቶች ጋር አክብbል፡፡
የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ አስተባባሪ አቶ አብርሃ አታሮ እንዳሉት ትምህርት ቤቶች ሰብአዊ መብትን በተመለከተ ህፃናት ተኮትኩተው የሚያድጉበት በመሆኑ የኮሚሽኑን አላማ ለማሳካት ትልቅ ፋይዳ አላቸው፡፡
መጪው ትውልድ ሰብአዊ መብቶችን ለማክበርና ለማስከበር የሚያስችለውን ስንቅ ከትምህርት ቤቶች ይቀስማል ብለዋል ፡፡
በሀገራችን ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ የሚከበረው የዓለም ህፃናት ቀን “ሁሉም ህፃናት ሰብአዊ መብቶችን በማከበር፣ በማስከበርና ሌሎችንም በማስገንዘብ ትምህርት ቤቶች ትልቅ ሚና አላቸው” የሚል መርህ አላው፡፡
በበአሉ አለም አቀፍ የህፃናት መብቶች ኮንቬንሽንን፣ የአፍሪካ ህፃናት ሰብአዊ መብትንና የኢትዮጵያ መንግስት ለሠብአዊ መብቶች የሠጠውን ትኩረት የሚዳስስ ጽሑፍ ቀርቧል፡፡
የበአሉ ተሳታፊ ህፃናቶች የተለያዩ ጭውውቶችንና ሥነ ጽሑፎችን አቅርበዋል፡፡
ትምህርት ቤቶች በሥነ ምግባር የታነፀ የሞራል እሴት ያለው፣ የነቃና ህግ አስከባሪ ዜጋ ለመፍጠር የሚያደርጉትን ጥረት ህብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት እንዲደግፉ ጥሪ ቀርቧል ፡፡ ባለደረባችን ደስታ ወ/ሰንበት እንደዘገበው፡፡http://www.smm.gov.et/_Text/11HidTextN305.html
የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ አስተባባሪ አቶ አብርሃ አታሮ እንዳሉት ትምህርት ቤቶች ሰብአዊ መብትን በተመለከተ ህፃናት ተኮትኩተው የሚያድጉበት በመሆኑ የኮሚሽኑን አላማ ለማሳካት ትልቅ ፋይዳ አላቸው፡፡
መጪው ትውልድ ሰብአዊ መብቶችን ለማክበርና ለማስከበር የሚያስችለውን ስንቅ ከትምህርት ቤቶች ይቀስማል ብለዋል ፡፡
በሀገራችን ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ የሚከበረው የዓለም ህፃናት ቀን “ሁሉም ህፃናት ሰብአዊ መብቶችን በማከበር፣ በማስከበርና ሌሎችንም በማስገንዘብ ትምህርት ቤቶች ትልቅ ሚና አላቸው” የሚል መርህ አላው፡፡
በበአሉ አለም አቀፍ የህፃናት መብቶች ኮንቬንሽንን፣ የአፍሪካ ህፃናት ሰብአዊ መብትንና የኢትዮጵያ መንግስት ለሠብአዊ መብቶች የሠጠውን ትኩረት የሚዳስስ ጽሑፍ ቀርቧል፡፡
የበአሉ ተሳታፊ ህፃናቶች የተለያዩ ጭውውቶችንና ሥነ ጽሑፎችን አቅርበዋል፡፡
ትምህርት ቤቶች በሥነ ምግባር የታነፀ የሞራል እሴት ያለው፣ የነቃና ህግ አስከባሪ ዜጋ ለመፍጠር የሚያደርጉትን ጥረት ህብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት እንዲደግፉ ጥሪ ቀርቧል ፡፡ ባለደረባችን ደስታ ወ/ሰንበት እንደዘገበው፡፡http://www.smm.gov.et/_Text/11HidTextN305.html
Comments
Post a Comment