በሲዳማ ዞን የአማራጭ ኢነርጂ ልማት በመጠናከር ላይ ነው



ሰሞኑን በሃዋሳ ከተማ በተካሄደው የደቡብ ክልል የውሃ ጉባኤ የቀረበው የ2004 /ም የመምሪያው የስራ ኣፈጻጸም የተመለከተው ኣንድሪፖርት እንዳመለከተው በዞኑ ውስጥ በኣማራጭ ኢነርጂ ልማት ዘርፍ ኣበራታች ስራዎች ተከናውነዋል።
መምሪያው በባጀት ኣመቱ ለማከናወን ካቀዳቸው 19 አዲስ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃ አምራቾች ማህበራት እንዲቋቋሙ በማድረግ ለ3- ማህበራት ፕሬስና ሞልድ ተገዝቶ ድጋፍ ማድረጉ የተገለጸ ሲሆን፤ 19 ወረዳዎች በ38 አማካይ ቦታዎች የማገዶ ቆጣቢ ምድጃ ላይ ለሕብረተሰቡ ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በመስጠት ከእቅዱ በላይ በመስራት 4500 የተሻሻሉ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎ አንዲሰራጩ በማድረግ በርካታ የዞኑን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ኣድርጓል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በሁሉም ወረዳዎች 100 የሚሆኑ የቤተሰብ የሶላር ተጠቃሚ ማህበራት መደራጀታቸው ሲገለጽ፤ የኃይል አማራጭ ኢነርጂ አጠቃቀም ላይ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል።
እንደሪፖርቱ ከሆነ የሶላር ኢነርጂ ተከላ እና የባዮ ጋዝ ግንባታ በተለያዩ ወረዳዎች የተካሄደ ሲሆን፤ ኣራት የአማራጭ ኢነርጂ ዳሰሳ ጥናት ተከናውነዋል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር