ካላ ደሴ ዳልኬ እና አቶ በረከት ስምኦንን ጨምሮ የመንግሥት ባለሥልጣናት በማስትሬት ዲግሪ ተመረቁ



•    አብዛኞቹ በምረቃው ዕለት አልተገኙም
በብርሃኑ ፈቃደ
ፕሮፌሰር ባደግ በቀለ በመሠረቱት ኢንተርናሽናል ሊደርሺፕ ኢንስቲትዩት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው በትናንትናው ዕለት ከተመረቁት መካከል፣ በሚኒስትር ማዕረግ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ በረከት ስምኦንን ጨምሮ በርካታ ባለሥልጣናት በማስትሬት ዲግሪ ተመረቁ፡፡ የማስትሬት ዲግሪያቸውን በትራንስፎርሜሽናል ሊደርሺፕ ዘርፍ የሠሩት አቶ በረከት በምረቃው ሥነ ሥርዓት አልተገኙም፡፡ እንደ አቶ በረከት ሁሉ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ አቶ ደሴ ዳልኬ፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዴኤታው ዶክተር አብርሃም ተከስተ መስቀልም ካልተገኙት መካከል ናቸው፡፡ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ ሞሐመድ ኡመር፣ በመከላከያ ሚኒስቴር የምዕራብ ዕዝ ኰማንደር ብርሃኑ ጁላ ገላቻን ጨምሮ በርካታ የመንግሥት ሹማምንት ተመርቀዋል፡፡

አቶ በረከት ለመመረቂያ ያቀረቡት ጽሑፍ እያደጉ ባሉ ልማታዊ መንግሥታት ላይ ያነጣጠረ ሲሆን፣ ‹‹Emerging Developmental States: Transformational Leadership in Governemnt›› በሚል ርዕስ በጻፉት መመረቂያቸው ዲግሪያቸውን እንዳገኙ ከኢንስቲትዩቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ 
http://www.ethiopianreporter.com/news/293-news/8093-2012-10-13-14-27-28.html

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር