ጃፓን ለሲዳማ ዞን የገንዘብ ድጋፍ ሰጠች
አዲስ አበባ, መስከረም 18 ቀን 2004 (አዲስ አበባ) - ጃፓን በኢትዮጵያ በሰብአዊ ደሕንነት ላይ ለሚካሔዱ ሁለት ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ የሚውል የ225 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ሰጠች፡፡
የገንዘብ ድጋፉን ለመስጠት ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ የጃፓን ኤምባሲ ከሲዳማ ዞን እና ሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎፕመንት ከተሰኝ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር ተፈራርሟል፡፡
ስምምነቱን በጃፓን በኩል የፈረሙት በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሒሮዩኪ ኪሽኖ፣ የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪው አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ እንዲሁ የሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎመንት ዳይሬክተር አቶ በላቸው ለማ ናቸው፡፡
የጃፓን መንግስት ለሰብአዊ ድህነነት ስራዎች ትኩረት የሚሰጥ ሲሆን ድጋፉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች እንደሚው አምባሳደሩ ጠቁመዋል
ጃፓን ከ1997 ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ በትምህርት፣ በመጠጥ ውሃና በሌሎችም መሰረታዊ የሰው ልጅ ፍላጎትን በሚያሟሉ ዘርፎች ከ300 በላይ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጓን አብራርተዋል፡፡
የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ እና የሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎመንት ዳይሬክተር አቶ በላቸው ለማ በዚሁ ወቅት የገንዘብ ድጋፉን በአግባቡ ለተፈቀደለት ስራ በማዋል ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡
የገንዘብ ድጋፉን ለመስጠት ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ የጃፓን ኤምባሲ ከሲዳማ ዞን እና ሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎፕመንት ከተሰኝ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር ተፈራርሟል፡፡
ስምምነቱን በጃፓን በኩል የፈረሙት በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሒሮዩኪ ኪሽኖ፣ የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪው አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ እንዲሁ የሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎመንት ዳይሬክተር አቶ በላቸው ለማ ናቸው፡፡
የጃፓን መንግስት ለሰብአዊ ድህነነት ስራዎች ትኩረት የሚሰጥ ሲሆን ድጋፉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች እንደሚው አምባሳደሩ ጠቁመዋል
ጃፓን ከ1997 ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ በትምህርት፣ በመጠጥ ውሃና በሌሎችም መሰረታዊ የሰው ልጅ ፍላጎትን በሚያሟሉ ዘርፎች ከ300 በላይ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጓን አብራርተዋል፡፡
የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ እና የሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎመንት ዳይሬክተር አቶ በላቸው ለማ በዚሁ ወቅት የገንዘብ ድጋፉን በአግባቡ ለተፈቀደለት ስራ በማዋል ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡
Comments
Post a Comment