Posts

ንግስት ፉራ

Image
በአበበ ከበደ የተተረከ ንግስት ፉራ ስመጥር የሲዳማ ንግስት የነበረች ሲሆን ሴቶችን ሁሉ መልካም ባህሪን ያስተማረችና እስካሁንም ድረስ ተቀባይነት ያላት ሴት ነች፡፡ ንግስቲቱ በጣም ብልህ ነበረች፡፡ በቅድሚያ ሴቶች ለወንዶች ሙሉ ለሙሉ ተገዢ እንዳይሆኑ፣ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ሴቶች ለወንዶች ሙሉ ለሙሉ ታዛዥ እንዳይሆኑ ትመክራቸው ነበር፡፡ ከዚያም በላይ ሴቶች አይን አፋር እንዲሆኑና ወንዶች እነርሱ ስለሚያስቡት ነገር ሁልጊዜም ግምታዊ እንጂ ግልፅ እንዳይሆን ታስተምራቸው ነበር፡፡ ሃፍረተ ገላቸውንም በአደባባይ እንዳያሳዩና ሰውነታቸውንም ከጉልበታቸው እስከ ወገባቸው ድረስ እንዲሸፍኑ ትነግራቸው ነበር፡፡ ወንዶች በውበት ስለሚማረኩ ሴቶች ራሳቸውን በደንብ እንዲጠብቁ ታስተምራቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ንግስት ፉራ ለወንዶች በጣም መጥፎ ሴት ነበረች፡፡ የማይቻሉ ነገሮችን ሁሉ እንዲሰሩ ታዛቸው ነበር፡፡ “ ወደ ወንዙ ሄደህ ውሃ በወንፊት አምጣ፡፡” እያለች ታዝ ነበር፡፡ ወይም በጣም ስስ ከሆነ ሳር ትልልቅ ገንዳዎችን እንዲሰሩ አለያም ከረጃጅም ፀጉሮቿ አንዱን ነቅላ ስድስት ቦታ እንዲሰነጥቁት በማዘዝ ወንዶችን ታሰቃያቸው ነበር፡፡ ከሁሉ በላይ ግን ራሰ በራና አጭር ወንዶችን አጥብቃ ትጠላ ነበር፡፡ ስለዚህ አጫጭር እንዲሁም ራሰ በራ ሰዎችን ሁሉ እንዲገደሉ ታዝ ነበር፡፡ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ አጫጭርና ራሰ በራ ሰዎች ሲገደሉ አንድ መላጣና አንድ ራሰ በራ ወንዶች ግን ከዚህ ችግር ተርፈው ነበር፡፡ አጭሩ ሰው ረጃጅም ተረከዝ ያሏቸው ጫማዎች በማድረግ ሲተርፍ ( ረጅም ተረከዝን የፈጠረው እርሱ ነው ) ራሰ በራው ሰው ደግሞ ሰው ሰራሽ ጸጉር ( ዊግ ) በማድረግ ከሞት ዳነ፡፡ ( ዊግን የፈጠረው ሰው እርሱ ነው፡፡ ) ታዲያ አጭሩና ራሰ በራው ሰዎች ንግስ

Unborn Hawassa Bank Requests Transfer of Equity to Berhan Bank

New Promoters of the under formation Hawassa Bank requested the central bank to transfer the equity contributions  of their shareholders to Berhan International Bank (BIB), one of the nine existing banks expected to fulfil the half a billion Birr threshold capital requirement after four years. National Bank of Ethiopia (NBE) raised the capital requirements for banks from 75 million to 500 million Br with the motive to create strong banks, in September 2011. The regulator’s directive put 13 private banks under formation, including Hawassa in limbo. Some of the banks have still not decided their fates, including some contemplating liquidation. Hawassa Bank started floating its shares in 2009, through 43 promoters, and was able to raise 20 million Br in capital from 530 shareholders. But, before it accomplished collecting the previously required amount, the central bank issued the new directive. The majority of the promoters were frustrated by the new capital requirement and gave

Why Sidama? There are many places around the world that need aid. So, why should you care about Sidama specifically? There are only two hospitals serving more than ten million people. Most residents have no access to any kind of healthcare.

http://www.fayyefoundation.org/ HOME ABOUT MEMBERS STAFF BOARD OF DIRECTORS WHY SIDAMA DONATE CONTACT Did you know? The most important source of income for Sidama is coffee. The area produces a large percentage of Ethiopia’s exported coffee. Help Support Fayye If you are interested in our cause and volunteering for our foundation please contact our volunteer coordinator. Volunteer Now >> How we make a difference There are two ways to help Fayye Foundation - either time or a donation. To learn more about each option please visit our  volunteer  or  how to donate  pages. We appreciate any help, no matter how big or small. Mission Statement The Fayye Foundation was created to address the orphan crisis in Sidama, Ethiopia. It is our mission to help end this tragedy by focusing on two areas where help is needed the most: maternal health for expecting mothers, and assistance to famili

Introducing... The Fayye Foundation!

Image
FRIDAY, MAY 11, 2012 Introducing... The Fayye Foundation! Wow, yesterday was quite a media storm for my girl Jamie and her controversial  Time Magazine cover !  If you're offended by the title, I implore you to read Jamie's  Q&A  with Time Magazine, to see that while she has chosen extended breast feeding for her family, she has the utmost respect for mothers who don't.  In fact, she's one of the most non-judgmental people I know.  She did not pick the title of the article!  Unfortunately her  personal blog  has been down due to traffic, but they're working hard to get it back up.  In the meantime, reporters and news media have been contacting me through our  Mommy Hates Chemicals blog, to try and get in touch with Jamie.  Thankfully Time Magazine is helping her out by assigning her a PR person to handle all the media.  She will be on the Today Show (today!) at the 9:ooam hour, being interviewed by Matt Lauer and will also be on Dateline tonight,

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የህግ ተማሪዎች የአምሳለ ፍርድ ቤት የክርክር ውድድር የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ

Image
አዋሳ, ሚያዝያ 29 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - ሰብአዊ መብት እንዲጎለብት ከትምህርት ሚኒስቴርና ከ18 ዩኒቨርስቲዎች ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ ከሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ለሶስት ቀናት ያዘጋጀው 4ኛ ብሄራዊ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የህግ ተማሪዎች የአምሳለ ፍርድ ቤት የክርክር ውድድር ትናንት ተጠናቋል፡፡ በውድድሩም የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ አጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል፡፡ የኮሚሽኑ የሴቶችና ህጻናት ኮሚሽነር ወይዘሮ አስማሩ በሪሁን በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ሰብኣዊ መብቶች በየደረጃው በሚገኙ የትምህር ተቋማት በስርዓተ ትምህርት እንዲካተት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመው ተግባራዊ እንቅሳቃሴ ተጀምሯል፡፡ እንዲሁም ከ18 የህግ ትምህርት ከሚሰጡ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ጋር ለመስራት ስምምነት ላይ በመደረሱ ከ110 በላይ ነጻ የህግ ማዕከላትን ከፍተው አቅም ለሌላቸው በተለይም ለሴቶች፣ ለህጻናት፣ ለአካል ጉዳተኞችና ለሌሎችም የህብረተስብ ክፍሎች አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም የህግ ትምህርት ከሚሰጡ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር የሰብአዊ መብት ግንዛቤን የማስፋት ስራዎች እየተከናወነ ከመሆኑም በላይ በህግ ተማሪዎች መካከል የአምሳለ ፍርድ ቤት የክርክር ውድድር በመቀሌ ፣ በጅማና በባህር ዳር ዩኒቨርስቲዎች አዘጋጅነት በተለያዩ ርዕሶች ላይ ላለፉት ሶስት አመታት መካሄዱን ገልጸዋል፡፡ ዘንድሮ ለ4ኛ ጊዜ ከሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር " የባህል መብቶችና የሴቶች መብት " በሚሉ ጉዳዮች ዙሪያ መካሄዱንና በተለይ በሴቶች መብት ላይ ተማሪዎች መሰረታዊ ዕውቀትና ክህሎት እንዲያዳብሩ መንገድ በማሳየት ለ

የኢጋድ አባል ሀገራት የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና አፋጣኝ ምላሽ ሜካኒዝምን (ሲዋርን CEWARN) አቋቋመው እንቅስቃሴ ከጀመሩ ወዲህ በቀጣናው ድንበር ዘለል ግጭቶች እየቀነሱ መጥተዋል ተባለ፡፡

የኢጋድ አባል ሀገራት የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና አፋጣኝ ምላሽ ሜካኒዝምን (ሲዋርን CEWARN) አቋቋመው እንቅስቃሴ ከጀመሩ ወዲህ በቀጣናው ድንበር ዘለል ግጭቶች እየቀነሱ መጥተዋል ተባለ፡፡የሜካኒዝሙ ጥረት በሀገራቱ መሀከል መተማመንና በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ አብሮ የመስራት ልምድ እንዲያዳብሩ አስተዋፅኦ ማበርከቱንም ገልጿል፡፡ ሜካኒዝሙ ለሚቀጥሉት 8 ዓመታት የሚመራበት አዲስ ስትራቴጂ በመንደፍ ላይ መሆኑን አመልክቷል፡፡የኢጋድ አባል ሀገራት በአርብቶ አደሩ አካባቢ የሚከሰቱት ድንበር ዘለል ግጭቶችን በማስወገድ አካባቢው አስተማማኝ ስላም ያለው የልማት ቀጠና ለማድረግ ነበር ከ9 ዓመታት በፊት የግጭት ቀድመ ማስጠንቀቂያና አፋጣኝ ምላሽ ሜካኒዝምን ያቋቋሙት፡፡ ሜካኒዝሙ በሀገሪቱ የሚገኘውን የመነገስት መዋቅርና ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ግጭቶች እንዳይከሰቱ ከተሰከቱም በአፋጣኝ ምላሽ እንዲያገኙ ሲሰራ ቆይቷል፡፡በኢትዮጵያ የሜካኒዝሙ የካራሞጃና የሶማሊያ ቅርንጫፎች ሜካኒዝሙ ለቀጣዩቹ 9 ዓመታት የሚመራበት አዲስ ስትራቴጂ ለመንደፍ በሀዋሣ ከተማ ባካሄዱት ስብሰባ ላይ እንደተገለፀውም በሁሉም ሀገራት በአርብቶ አደሩ አካባቢዎች አንፃራዊ ሰላም እየሰፈነባቸው መጥቷል፡፡ የሜካኒዝሙ ዳይሬክተር ዶክተር ማርቲን ኪማኒ እንዳሉት በሀገሪቱ እስከ ቀበሌ ደረጃ መዋቅሮችን በመዘርጋት ባህላዊና ዘመናዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎችን በመጠቀም ድንበር ተሻጋሪ ግጭቶች በከፍተኛ ሁኔታ ለመከላከል ተችሏል፡፡በቀጣናው በተፈጥሮ ሀብት፣ በግጦሽ፣ በውሃ፣በባህላዊ ተፅዕኖና ሌሎች ምክንያቶች አልፎ አልፎ ግጭቶች ሲከሰቱም ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል አቅም ተፈጥዋል ብለዋል፡፡ አባል ሀገራቱ ግጭቱን ለማስወገድ ፈጣን የመረጀ ልውውጥና የጋራ አፈተት ስልቶች ማዳበራ

EEPCO wins in Arba Minch, St. George held in Hawassa

Image
Addis Ababa, Ethiopia  – EEPCO and Dedebit FC are closing in on current Ethiopia Premier League leader St. George, who was held scoreless in Hawassa. EEPCO scored a valuable 1-0 away victory against Arba Minch, while defending champion Ethiopian Coffee and Defence Force played to a 1-1 draw here in Addis. With one match in hand, St. George is still in the lead with 43 points followed by Dedebit FC and EEPCO, who accumulated 39 points each. Week 19 Results: Tuesday, April 24, 2012 Dire Dawa City 1-0 CBE Thursday, April 26, 2012 Arba Minch 0-1 EEPCO Hawassa City 1-1 St. George Ethiopian coffee 1-1 Defence Force League Table Standings: Rank Teams Played Wins Draw Lost Diff GD Points 1 Saint George 18 13 4 1 27 – 4 23 43 2 Dedebit FC 19 12 3 4 35 – 13 22 39 3 EEPCO FC 19 11 6 2 32 – 14 18 39 4 Hawassa City FC 19 6 10 3 18 – 15 3 28 5 Mugher Cement 19 6 8 5 22 – 22 0

በማንኛውም ቦታ የሚለበስ የሲዳማ ባህላዊ ልብስ

Image
የፋሽን ኢንዱስትሪ እየተስፋፋ ከመጣበት ዘመን አንስቶ በርካታ የአለባበስ ልምዶችም አብረው ተፈጥረዋል። በተለይ በአውሮፓውያኑ አካባቢ አንድን ልብስ ከመምረጣቸው በፊት ለምን ጉዳይ እንደሚለብሱትና በምን ወቅት እንደሚያዘወትሩት ጠንቅቀው ማወቅ ይጠበቅባቸዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህም በአገራችን የሚዘጋጁ ባህላዊ አልባሳት ጊዜና ቦታ ተመርጦላቸው እንዲለብሱ እየሆነ ነው። ብዙ ጊዜ የባህላዊ አልባሳት በበዓላት ቀን ላይ ብቻ እንዲለበሱ የተወሰኑ ነበሩ። አሁን አሁን ግን የባህላዊ አልባሳትን በዘመናዊ መንገድ በማዘጋጀት በተለያዩ ወቅቶች በማንኛውም ቦታ እንዲለበሱ እየደተረገ ነው። በሐዋሳ ከተማ የሚገኘው አበባ ሹራብና ባህላዊ አልባሳት ማምረቻና ማከፋፈያም ከአገራችን አልፎ እስከ ውጭ አገር ድረስ ባህላዊውን አልባሳት በዘመናዊ መንገድ በማዘጋጀት ዕውቅናን እያተረፈ መጥቷል፡፡  ዋና ሥራ አስኪያጇ ወይዘሮ አበባ ዘነበር እንደ ገለጹልን፣ የባህላዊ አልባሳት በዘመናዊ መንገድ በመዘጋጀታቸው ፈላጊያቸው መብዛቱን ነው። ለዛሬ ሊያስተዋውቁን የወደዱት በሲዳማ የባህል ጨርቅ የሚሠራውን ሸሚዝ ወይም የሱሪ አላባሽ ነው። ልብሱ የሚሠራው የሲዳማ ባህላዊ አልባሳት ከሚጠቀምባቸው ሦስት ቀለሞች አንዱ በሆነው በቀይ ቀለም ነው። የጨርቁ ምርት ሳባ ይባላል። አሠራሩ ብዙዎች እንዲጠቀሙበት በማሰብ በአፍሪካውያን አለባበስ ዲዛይን ተደርጓል። ሰፋ ያለና ለሁሉም ሰው እንዲያመች ተደርጐ ተዘጋጅቷል። ሸሚዙን ወፍራምም ሆነ ቀጭን ሰው፤ ወንድም ሆነ ሴት በማንኛውም ጊዜና ቦታ ሊለብሰው ይችላል። «ወንዶች ከመረጡት ሱሪ ጋር ሴቶች ደግሞ በጂንስና በታይት ቢለብሱት የበለጠ ውበታቸውን ያጐላላቸዋል» የምትለው ዲዛይነር ወይዘሮ አበባ፣ በተለይ በሙቀት ወቅት ቢለበስ የበለጠ ምቾትን ይሰ

በሲዳማ ዞን የቦርቻ ወዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት የወባ በሽታን በመከላከልና በመቆጣር ረገድ የአንድ ለእምስት ትስስር ስኬታማ ውጤት እያስገኘ መሆኑ አስታወቀ:

በሲዳማ ዞን የቦርቻ ወዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት የወባ በሽታን በመከላከልና በመቆጣር ረገድ የአንድ ለእምስት ትስስር ስኬታማ ውጤት እያስገኘ መሆኑ አስታወቀ::ጽህፈት ቤቱ ሰሞኑን ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ የወጡ ቀበሌያትን ባስመረቀበት ወቅት የጽህፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ ዱባለ ባራሳ እንዳስታወቁት በወረዳው በሚገኙ 42 ቀበሌያት በአንድ ለአምስት ትስስር በተደረገው ጥረት 16ቱን ጤና ፖኬጅ ተግባራዊ በማድረግ አበረታች ውጤት ማየት ተችሏል:: ለውጤቱ መገኘትም የጤና ልማት ሠራዊት በአንድ ለአምስት ትስስር መሠረታዊ የግል ንጽህና፣ የአካባቢ ጤና አጠባበቅ ፣ የቤተሰብ ጤና አገልግሎት እንዲሁም የወባ በሽታን በመከላከልና በመቆጣጠር ቀዳሚ ተዋናይ መሆናቸውን ተናግረዋል:: በተይም የጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞች ፣በጎ መልክተኞችና የጤና ባለሙያዎች ድርሻ የጎላ መሆኑን ኃላፊው ገልፀው በጥረቱም 9 ሺህ ሞዴል ቤተሰብ መፍጠር መቻሉንም ጠቁመዋል:: የዞኑ በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ኢማላ ላማቻ በበኩላቸው ህብረተሰቡ ግንባር ቀደም ተዋናይና በማህበረሰብ ውይይት ንቁ ተሳትፉ በመሆን ጤናውን ማጐልበት እንደሚገባው የዞኑ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ እንደዘገበው::

በሲዳማ ዞን ሐዋሣ ዙሪያ ወረዳ አርሶ አደሮች የሐዋሳ ሐይቅንና ጥልቀት የሌላቸው ጉድጓዶችን በመጠቀም ከ800 በላይ ሄክታር መሬት በአነስተኛ መስኖ አልምተው ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት አስታወቀ:

በሲዳማ ዞን ሐዋሣ ዙሪያ ወረዳ አርሶ አደሮች የሐዋሳ ሐይቅንና ጥልቀት የሌላቸው ጉድጓዶችን በመጠቀም ከ800 በላይ ሄክታር መሬት በአነስተኛ መስኖ አልምተው ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት አስታወቀ::ተጠቃሚ አርሶ አደሮቹ እንደተናገሩት በአመት 4 ጊዜ የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችንና ወቅታዊ ሰብሎችን በማምረት እስከ 1 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘት ችለዋል:: የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ክፍሌ ሻሾ እንደገለጹት በመስኖው ልማት ከ2ሺ 500 በላይ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ሆነዋል::በመንግሥት ድጋፍ የተገኙትን 20 የውሃ መሣቢያ ሞተሮችን በ1ለ5 ትስስር ለተደራጁ አርሶ አደሮች በማከፋፈል ዓመቱን በሙሉ ዝናብ ሳይጠብቁ በማምረት ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ አስረድተዋል:: አርሶ አደሮቹ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመን፣ ሽንኩርትና ቃሪያ ከሚያለሙዋቸው ምርቶች ዋና ዋናዎቹ ናቸው ብለዋል::በአሁኑ ጊዜ ማሳ ላይ ከሚገኘው ምርትም ከ1 ሚሊዮን በላይ ኩንታል ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ክፍሌ ገልፀዋል ሲል የሲዳማ ዞን የመ/ኮ/ጉ/መምሪያ ዘግቧል :: Back

በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት/ኢጋድ/ አባል ሀገራት አዲስ እቅድ ላይ የሚነጋገር አውደ ጥናት በሀዋሳ ተጀመረ

Image
New አዋሳ, ሚያዝያ 23 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት/ኢጋድ/ አባል ሀገራት ተግባራዊ የሚደረገው አዲሱ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና አፋጣኝ ምላሽ ስልት ስትራቴጂክ ዕቅድን ለማዳበር ኢትዮጵያ የበኩሏን አስተዋጾኦ እያበረከተች መሆኗ ተገለጸ፡፡ በስትራቴጅክ ዕቅዱ ላይ ለመምከርና ሀሳብ ለማሰባሰብ የተዘጋጀ አውደ ጥናት ትናንት በሃዋሳ ከተማ ሲጀመር የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ምትኩ ካሳ እንደገለጹት በአፍሪካ ቀንድ በተለይ በኢጋድ አባል ሀገራት የሚከሰቱ ግጭቶች ለልማት፣ለመልካም አስተዳዳርና ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት አሉታዊ ተጽልኖና ጫና እያሳረፉበት እንዳለ ይታወቃል፡፡ የግጭቶች መንስኤ እንደ ሰዎች ፍላጎትና ባህሪ ተለዋዋጭ መሆናቸውን ገልጸው ችግሮቹ በኢትዮጵያና በጎረቤት ሀገር በአርብቶ አደር አካባቢ ለጥሎሽ የሚጠየቀውን ከብት ከሌላ ጎሳ ለማምጣት መሞከር፣ውሃና ግጦሽ ፍለጋ ፣የተመጣጠነ የሀብት ጉድለት የመሳሳሉ ችግሮች መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ ለኢትዮጵያና ለቀሩትም የኢጋድ አባል ሀገራት ትልቁ ጠላት ድህነት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው የሚከሰቱ ግጭቶች ከድህነት ጋር የተያያዙ በመሆናቸው ችግሮቹን ከምንጫቸው ለማድረቅ እንደያአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ህብረተሰቡን ባሳተፈ ሁኔታ አዲስ የጋራ ስትራቴጂክ ዕቅድ እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ቀደም ሲልም ከሌሎች የኢጋድ አባል ሀገራት ጋር በመተባበር የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና አፋጣኝ ምላሽ ስልት እንዲቋቋም ግምባር ቀደም ሚና በመጫወት ድንበር ተሻጋሪ የአርብቶ አደር ግጭቶችን በመከላከልና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ስትንቀሳቀስ መቆየቷን ተናግረዋል፡፡ ላለፉት አምስት አመታት የቆየው ፕሮግራም በቅ