ኢትዮጵያና ሩሲያ ወታደራዊ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
- ልዩ ኢኮኖሚያዊ ትብብሮችን ለማድረግም አቅደዋል ኢትዮጵያና ሩሲያ ለዓመታት የቆየ ትብብራቸውን በተለይም ወታደራዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ከመግባባት ላይ ደረሱ፡፡ ሁለቱ አገሮች የመግባባት ስምምነት ላይ የደረሱት የሩሲያው የረዥም ጊዜ ዲፕሎማትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሰርጌይ ላቭሮቭ ባለፈው ሐሙስ ለአንድ ቀን የሥራ ጉበኝት አዲስ አበባ በመጡበት ወቅት ነው፡፡ ሰርጌይ ላቭሮቭ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በደረሱበት ወቅት የተቀበሏቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ናቸው፡፡ በመቀጠልም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በሁለቱ አገሮች የጋራ ጉዳይ ላይ ከሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መክረዋል፡፡ ከሁለቱ አገሮች ባለሥልጣናት ምክክር በኋላ ለጋዜጠኞች የተካሄደው ውይይት የገለጹት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሰርጌይ ላቭሮቭ፣ በተለያዩ የሁለቱ አገሮች የጋራ ትብብሮች ላይ መምከራቸውን፣ ከእነዚህም መካከል በወታደራዊ ትብብርና በልዩ ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶች ለመተባበር መግባባታቸውን ገልጸዋል፡፡ ባለፈው ሐምሌ ወር የሁለቱ አገሮች ከፍተኛ ባለሥልጣኖች በጋራ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ ተገናኝተው በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ በኢነርጂ፣ ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረትና የኢንቨስትመንት ጥበቃ ለማድረግ መስማማታቸውን የገለጹት ሰርጌይ ላቭሮቭ፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ጋር ተግናኝተው በተነጋገሩብት ወቅት የተጠቀሱት የትብብር መስኮች በፍጥነት እንዲተገበሩ ለማድረግ መስማማታቸውን አስረድተዋል፡፡ ይህ ሲባል ሌሎች ጉዳዮች የሉም ማለት እንዳልሆነ የተናገሩት ሚኒስትሩ፣ በተለይ የሁለቱ አገሮች ግንኙነት መገለጫ ባህሪ የሆነው ወታደራዊ ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል መስማማታቸውን አስታውቀዋል፡፡ ዶ/ር ቴድሮስ በበኩላቸው